በኢትዮጵያ በነገው እለት ስድስት ልጆቻቸውን በአንድ ቀን የሚድሩት ወላጆች የደስታ መልዕክት እየጎረፈላቸው ነው ጥንዶቹ አቶ ተፈሪ እና ወ/ሮ የሺማጫሽ ጣሰው በኦሮሚያ ክልል ጎሃፂሆን ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ የዘጠኝ ልጆች ወላጆች ናቸው።ከነዚህ ውስጥ ስድስቱ በነገው እለት ይዳራሉ።ከ1ኛ እስከ 6ኛ ወይንሸት ተፈሪ፣ ገነት፣ ዳምጠው፣ፍቅሩ፣ ትግስት፣ አዳነች ተፈሪ ይባላሉ።
ለሰርጉ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን እስከ 15 በሬ የታረደ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩ እንግዶች ይታደማሉ።