Get Mystery Box with random crypto!

♒Orthopedic Surgery in Ethiopia ♒

የቴሌግራም ቻናል አርማ ourpatients — ♒Orthopedic Surgery in Ethiopia ♒ O
የቴሌግራም ቻናል አርማ ourpatients — ♒Orthopedic Surgery in Ethiopia ♒
የሰርጥ አድራሻ: @ourpatients
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 313
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል በአጥንት ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስቶች የሚሠጡ ጠቃሚ ትምህርቶች እና የታካሚዎች ገጠመኞች ለአንባቢያን ይቀርብበታል።

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-05 21:07:22
2.2K views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 06:08:29

1.9K views03:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 21:22:05
2.0K views18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 21:21:50 ሳይወድቁ የተሠበሩት የ92 ዓመት ታካሚ!
——————————————————
ዶ/ር ሠዒድ መሐመድ (የአጥንት ስፔሻሊስት)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሠሞኑን ቀዶ ህክምና ከሠራሁላቸው ታካሚዎች ውስጥ እንደተለመደው ገጠመኙ ትምህርት ይሠጣል ብዬ የገመትኩትን ላካፍላችሁ ነው…

የራጁ ምስል የዘጠና ሁለት ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ የሆኑ ታካሚዬ የዳሌ መገጣጠሚያን የሚያሳይ ሲሆን፣ በግራ በኩል ያለው ("Before" image) የዳሌ መገጣጠሚያቸው አንገት (femoral neck) እንደተሠበረ ያሳያል። በቀኝ በኩል የሚገኘው ("after" image) ደግሞ የዳሌ መገጣጠሚያ ቅየራ (hip replacement) ከሠራሁላቸው በኋላ አርቴፊሻል መገጣጠሚያውን የሚያሳይ ነው።

እንደዚህ አይነት ከፍተኛ ቀዶ ህክምና የሚያስፈልጋቸው ጉዳቶች በመሠረቱ ከፍተኛ አደጋን ተከትለው የሚከሠቱ ቢሆንም፣ በዕድሜ የገፉ አዛውንቶች ላይ ሲሆን ግን ብዙውን ጊዜ ሻወር ሲወስዱ እንደ መውደቅ አይነት ቀላል አደጋዎችን ተከትለው ሲከሠቱ ይስተዋላል። የዛሬውን ባለታሪካችንን ገጠመኝ ግን "ትምህርት ሠጪ" ያስባለው እና ለመተረክ ያበቃው ግን የተለመደው አይነት "ቀላል የመውደቅ አደጋ" እንኳን ሳይደርስባቸው በመሠበራቸው ነው። ነገሩ እንዲህ ነው…

አዛውንቱ አባት በደረሰባቸው ከፍተኛ የሳንባ ኢንፌክሽን እና ኢንፌክሽኑን ተከትለው በተከሠቱባቸው ሌሎች ችግሮች ምክንያት ከሁለት ወራት በላይ ተኝተው እየታከሙ ስለነበረ ለረጅም ጊዜ ሳይንቀሳቀሱ በመቆየታቸው ምክንያት ፣ በእርጅና ጥንካሬውን ያጣው አጥንታቸው ይበልጥ ሊሳሳ ችሏል። አገገሙ ከተባለ በኋላ እንኳን ከአልጋ የሚወርዱት መፀዳጃ ቤት ለመጠቀም ብቻ፣ እሱም በአስታማሚዎቻቸው (ልጆቻቸው) እገዛ ነበር።

ከአንድ ወር በፊት  ታዲያ አንድ ልጃቸው ለሽንት ብሎ ከአልጋ ላይ ሊያወርዳቸው ሲሞክር ያለምንም ይህ ነው የሚባል አደጋ፣ እግራቸው በአልጋው ጠርዝ ንክኪ ምክንያት ድንገት ስለዞረባቸው ብቻ  ከፍተኛ ህመም ተሰምቷቸው ወደ አልጋቸው ሊመልሳቸው ተገደደ። ራጅ ሲነሱም ከላይ የጠቀስኩት ከፍተኛ ጉዳት እንዳላቸው ታወቀ። ደግነቱ ጊዜው የአጥንት ህክምና በቴክኖሎጂ እና ዘመናዊ አርቴፊሻል መገጣጠሚያዎች የተደገፈበት ጊዜ ስለሆነ በአጭር ጊዜ አገግመው ዳግም ለመራመድ የበቁ ቢሆንም፣ ክስተቱ ግን ቢያንስ ለሌሎቻችን ትምህርት ሊሆን ይገባል።

——————————————————
Take home message:
* የአልጋ ቁራኛ አዛውንቶች አጥንት ያለአደጋም ሊሠበር ስለሚችል፣ አስታማሚዎች ልዩ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል። መራመድ እስኪጀምሩ ድረስም፣ የአጥንታቸውን ጥንካሬ ለማቆየት ከምግብ ተጨማሪ ሰፕሊመንቶች ያስፈልጓቸዋል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
Follow us on:
YouTube: " Doctor Seid"
የቴሌግራም ቻናል: https://t.me/patientstories
የፌስቡክ ገፅ: የአጥንት ህክምና/Orthopedic Surgery (https://www.facebook.com/EthioOrthopedics/)
ስልክ: +251930099067/ +251935402078
1.8K views18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 18:35:50 አሳሳቢው የትምህርት ቤት ክሊኒኮች ጉዳይ!
———————————————————
ዶ/ር ሠዒድ መሐመድ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ክሊኒኮች ተማሪዎች ላይ የሚደርሱ ድንገተኛ የመፈንከት ወይም ሲወድቁ የመጎዳት ገጠመኞችን ለማከም፣ አልያም እንደ ስኳር ህመም፣ የነርቭ ህመም፣ ወዘተ… የመሳሰሉ የተለያዩ ህመሞች ያሉባቸው ተማሪዎች ላይ ድንገት ሊደርሱ የሚችሉ አደጋዎችን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታሉ።

ሠሞኑን የገጠመችኝ ታካሚ የ 12 ዓመት ታዳጊ ናት። ልጅቷ በተለምዶ "የሚጥል በሽታ" እየተባለ የሚታወቀው ህመም (epilepsy) ተጠቂ ስትሆን፣ አስኮ አካባቢ የሚገኝ አንድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የስድስተኛ ክፍል ተማሪ ናት። በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ አካባቢ ታዲያ ትምህርት ቤት ውስጥ ድንገት ራሷን ስታ ስትወድቅ ለስም ብቻ የተቋቋመው  እና ተማሪዎቹ እንደነገሩኝ እምብዛም ተከፍቶ አይተውት የማያውቁት የተማሪዎች ክሊኒክ እንደተለመደው ዝግ ስለነበረ አዝለዋት ከግቢ በመውጣት ወደ ህክምና ተቋም ሲሮጡ ትወድቅባቸውና እጇ ላይ ሌላ ጉዳት ይደርስባታል። ከነቃች በኋላ መንገድ ላይ የተጨመረውን መጀመሪያ ያልነበረ የአጥንት ጉዳት ለማሳከም ሌላ ውጣውረድ አስፈለገ።

የዕድል ጉዳይ ሆኖ እንጂ የልጅቷን አወዳደቅ እንደነገሩኝ ሙሉ በሙሉ ራሷን ስታ ስለነበረ ስትወድቅባቸው ጭንቅላቷ ከመሬት ጋር በመላተሙ ለጭንቅላት ደም መፍሰስ አደጋ የመጋለጥ ዕድሏ ሠፊ እንደነበረ ተረድቻለሁ። ወላጆቿ ለአጥንቷ ጉዳት ህክምና ሲያመጧት ምን ያህል ስሜታቸው ተጎድቶ እንደነበረም አትጠይቁኝ።

የልጅቷን ህይወት ለአደጋ ያጋለጠው ይህ ክስተት የተፈጠረው የትምህርት ቤቱ ክሊኒክ በስራ ላይ ባለመገኘቱ እንደነበረ ሳስብ ግን ጉዳዩ በሐገር አቀፍ ደረጃ ትኩረት የሚሻ እንደሆነ ለማስታወስ ወደድኩ። ለመሆኑ የትምህርት ቤት ክሊኒኮች አስፈላጊነታቸው ታውቆ በግብአት እና በባለሙያ ተደራጅተው አገልግሎቶች ስለመስጠት አለመስጠታቸው የሚከታተላቸው አካል ይኖር ይሆን?

ከእንደነዚህ አይነት አጋጣሚዎች ትምህርት መውሰድ ያስፈልጋልና ወላጆች ጉዳዩን ለመንግሥት ብቻ ከመተው ልጆቻችሁ የሚማሩባቸውን ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ክሊኒክ ለመገምገም ሞክሩ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
Follow us on:
YouTube: " Doctor Seid"
የቴሌግራም ቻናል: https://t.me/patientstories
የፌስቡክ ገፅ: የአጥንት ህክምና/Orthopedic Surgery (https://www.facebook.com/EthioOrthopedics/)
1.4K views15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 14:09:31
1.9K views11:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 14:09:21 ማስታወሻ ለኢትዮጲያ ህክምና ማህበር (EMA)
———————————————————
ዶ/ር ሠኢድ መሐመድ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሠሞኑን ከአንድ የኩላሊት ህክምና ስፔሻሊስት የስራ ባልደረባዬ ጋር ሁለታችንም ስለምናውቃቸው ስለአንድ ታካሚ ጉዳይ ስንወያይ ነበር። ታካሚዋ አስቸኳይ የኩላሊት እጥበት ህክምና እንደሚያስፈልጋቸው በተለያዩ የኩላሊት ስፔሻሊስት ሐኪሞች ቢነገራቸውም ውሳኔውን መቀበል (ሐኪሞቹን ማመን) አልፈለጉም። ከእርሱ በፊትም ሆነ ከእርሱ በኋላ ሌሎች ስፔሻሊስቶችን ሲያማክሩ፣ የሁሉም ውሳኔ ተመሳሳይ ቢሆንም ውሳኔውን መቀበል ተቸግረው ከሐገር ውጪ ሄደው የውጭ ሃኪሞችን ማማከር በመፈለጋቸው እስከአሁን እጥበት እንዳልጀመሩ አጫወተኝ። የጤናቸው ሁኔታም ቀናት በጨመሩ ቁጥር እየከፋ በአሁኑ ሰአት የውጪው ፕሮሰስ እስኪሳካ ህይወታቸው ለአደጋ ተጋልጧል።

ይህንን መሠል ገጠመኞች በየስፔሻሊቲ ዘርፉ የሚያጋጥሙ ናቸው። በዚህ በሐኪም እና ታካሚ ያለመተማመን ሂደት ውስጥ ግን ዋነኛ ተጎጂው ልክ ከላይ እንደጠቀስኩት ምሳሌ ታካሚው (ህብረተሰቡ) ነው። ይህ ችግር ከየት መጣ? ካልን ግን የችግሩ መንስኤ ከስንት አንድ ጊዜ የሚከሰቱ እና በየትኛውም ዓለም የሚያጋጥሙ የህክምና ስህተቶችን ከሚገባው በላይ በማጋነን እና የሆነውንም ያልሆነውንም በመጨማመር፣ ከዚያም አልፎ የኢትዮጲያዊያን የጤና ባለሙያዎች ብቻ ችግር አስመስለው የሚያቀርቡ ሚዲያዎቻችን ዋነኛ ተጠያቂዎች ናቸው።

በእኔ እይታ ሁለተኛው ተጠያቂ ደግሞ በጤና ባለሙያዎች ላይ ያልተገባ ውሸት ሲነዛ እና የበሬ ወለደ አሉባልታ ሲወራ ምንም እንደማይመለከታቸው እጃቸውን አጣጥፈው የሚመለከቱት የህክምና ማህበራት ናቸው። በኢትዮጵያ ውስጥ ከዋናው የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር (EMA) ጀምሮ በተለያዩ ስፔሻሊቲዎች እና የሙያ ዘርፎች ተደራጅተው ህጋዊ ሠውነት ያላቸው ማህበራት (societies) ቢኖሩም የሁሉም ሚና አመታዊ ስብሰባ ከማዘጋጀት እና ከአጫጭር ስልጠናዎች የዘለለ አይደለም። አለመታደል ሆኖ ይህ ባህል ከድሮውም በጤና ማህበራት የተለመደ ሆነ እንጂ፣ እንደ ሙያ ማህበርነታቸው፣ ሙያቸው ላይ ወይም አባላቶቻቸው ላይ ከመንግስትም ይሁን ከግለሰብ ወይም ከሚዲያ ተቋማት የሚደርሱ የህግ ጥሰቶችን ተከታትለው ክስ በመመስረት በመዋጮ የሚያኖሯቸውን አባላቶቻቸውን እና ሙያቸውን ማስከበር መሠረታዊ ተግባራቸው ሊሆን ይገባ ነበር።

ለአብነት ያህል ሰሞኑን አርቲስት ሃና ዩሐንስ አንዲት በካንሰር ህመም ምክንያት እግሯ በቀዶ ህክምና እንዲወገድ የተደረገላትን የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ታካሚ ጋብዛ ባደረገችው ቃለ ምልልስ ሁለቱም እየተቀባበሉ የሚያወሩት የጤና ባለሙያዎቹ ምን ያህል ሥነምግባር የጎደላቸው እንደሆኑ፣ ምን ያህል ዕውቀት እንደሌላቸው፣ ወዘተ… ነው።

ይህንን መነሻቸውን ለማጠናከርም በተለይም ታካሚዋ በቀዶ ህክምና ወቅት ደረሰብኝ ያለችውን የነርቭ ጉዳት አርቲስት ሃና ሙሉ ለሙሉ በመቀየር እና ተመልካችን ለመሳብ ምስሉ ላይ እንደምትመለከቱት "በስህተት እግሬን ቆረጡት" በሚል ነጭ ውሸት ቀይራ አቅርባዋለች። ርዕሱ ገርሞኝ ቪዲዮውን ስመለከተው ግን ሃና ልጅቷን ያከሟት ሐኪሞች (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል) "በስህተት እግሯን ቆረጡ" የሚል መልዕክት እንዲኖረው አድርጋ ያቀረበችው ክስተት በፍፁም ያልተከሰተ ከመሆኑም በላይ፣ ልጅቷ የምትገልፀው ከነአካቴው እግር የማስወገዱ ቀዶ ህክምና የተካሄደው ደቡብ አፍሪካ እንደሆነ ፣ ያከሟት ሃኪሞችም ያንን ያደረጉት በስህተት ሳይሆን በካንሰር ምክንያት በመሆኑ በመቁረጣቸው ህይወቷን እንዳተረፉ ነው። በበኩሌ በስህተት እግር መቁረጥን የሚያክል ዕምነት የሚያጠፋ ከባድ ዜና እንደቀልድ ዋሽቶ መለጠፍ ያለተጠያቂነት ማለፍ አለበት ብዬ አላምንም።

አርቲስቷ ይሄንን ትኩረት የሚስብ የቪዲዮ አርዕስት ስትመርጥ ያሳሰባት "ስንት ሰው የሄንን ቪዲዮ ተመልክቶ ምን ያህል ገንዘብ አገኝ ይሆን?" የሚለው ነው እንጂ በዚህ ውሸቴ ምክንያት በሚበላሸው የታካሚ እና የሐኪም ግንኙነት የስንት ሰው ህይወት ይበላሽ ይሆን? የሚለው አይደለም። ይሄንን ድፍረት ያገኘችውም ሁሉም የፈለገውን ያህል ዋሽቶ ሲጠቀም እንጂ ተጠያቂ ሲሆን ስላላየች ነው። ታዲያ ለምሳሌ እንኳን በዚህ ቪዲዮ ላይ ስማቸው እንዲጠለሽ የተደረጉትን ባለሙያዎች በአባልነት ያቀፉ ተቋማት (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፣ የኢትዮጵያ የአጥንት ህክምና ማህበር፣ የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር) በዚህ ጉዳይ ዝምታን መምረጥ አለባቸው?

በተለይም የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር (EMA) እንደዚህ አይነት በህዝብ ዘንድ ያላቸውን ዕውቅና ተጠቅመው ሙያውን የሚያጠለሹ አርቲስቶችን እና ጋዜጠኞችን ወደህግ በማቅረብ አንድም ለሚዲያ ባላቸው ቅርበት ምክኒያት የባለሙያውን ስም ዳግም እንዳሻቸው እንዳያጎድፉ ማድረግ፣ በሌላ በኩልም እንደነዚህ ያሉ ታዋቂ ግለሰቦች ወደህግ ቢቀርቡ ዜናው በቀላሉ ስለሚዳረስ ሁሉም ዜናው የደረሰው አካል የጤና ባለሙያዎችን በሐሰት ከመዝለፉ በፊት ቆም ብሎ እንዲያስብ መማሪያ ይሆናልና ጉዳዩ በዝምታ እንዳይታለፍ እጠይቃለሁ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
Follow us on:
YouTube: " Doctor Seid"
የቴሌግራም ቻናል: https://t.me/patientstories
የፌስቡክ ገፅ: የአጥንት ህክምና/Orthopedic Surgery (https://www.facebook.com/EthioOrthopedics/)
1.7K views11:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ