Get Mystery Box with random crypto!

ካህን ታፍኖ ታሥሮ ዝም የሚል ሲኖዶስን መንፈስ ቅዱስ ይመራዋል ብለን አናስብም፤ አንጠብቅምም። አባ | ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ካህን ታፍኖ ታሥሮ ዝም የሚል ሲኖዶስን መንፈስ ቅዱስ ይመራዋል ብለን አናስብም፤ አንጠብቅምም።
አባቶቻችን እውነት በመምህሩ መታሠር እጃችሁ ከሌለበት የታሠሩት የጉባኤ መምህር ናቸውና ዝምታችሁን አስወግዱ። ካልሆነ ግን እናንተን የሚተቹትን እየመረጣችሁ የምታሣሥሩ እናንተ ናችሁ።
በርግጥ የተወሰኑ አባቶች በጨለማው ሲኖዶስ ውስጥ ሆነው የሚሠሩትን ሥራ እያየን ነው። ጊዜ እንጠብቅ ብለን እንጂ ሀሉንም እንገልጠዋለን።
መንፈስ ቅዱስ የሚመራችሁ ከሆነ ኪህናችሁን አስፈቱ፤ ካህኑን የሚያሣሥር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው አካል የለምና ዝምታችሁን ስበሩ።
ትናንት በምእመን የተጀመረው እሥራት ዛሬ ካህን ላይ ደርሷል። ቀጣዩ ተራ የእናንተው ነው። የሚያዋጣው ከምትመሩት ምእመን ጋር መሆን ነው።
የምእመናን ጅረት አይቋረጥም፤ ፖለቲካ ግን ነገ ይጠፋል።

ድምፀ ተዋሕዶ

http://t.me/ortodoxtewahedo