2023-04-10 08:49:56
የወደመውን የደብረ መድኃኒት ሰብሸንጎ መድኃኒአለም ቤተ ክርስቲያንን መልሶ ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ ተጣለ።
የወደመውን የደብረ መድኃኒት ሰብሸንጎ መድኃኒአለም ቤተ ክርስቲያንን መልሶ ለመገንባት ዛሬ በ27/7/2015 ዓ/ም በዕለተ ቀኑ በብፁ አቡነ ዲዮናስዮስ የምስራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፀሎተ ቡራኬ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ።
በእለቱ በዓሉንም ለማክበርና የአባታችንን ቡራኬ ለመቀበል ጭምር እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝበ ምእመን ተገኝቷል።
ዕለቱ የአመቱ መድኃኔ ዓለም ስለነበር ታቦቱ ወጥቶ ህዝበ ምእመኑን ባርኳል።
በእለቱ ስለክብረ በዓሉ ከሀገረ ስብከት በመጡ ሰባክያንና በብፅዑ አባታችን የምእመኑን መንፈስ የሚያፀናና ከሀዘኑ የሚያረጋጋ ጥዑም ትምህርት ተሰጥቷል።
በመርሀ ግብሩም መሰረት አጭር የሥራና ግልፅ የገቢ አሰባሰብ ሪፖርት ቀርቧል።
ብፅዑ አባታችንና ሰባክያን ከቀረበው ሪፖርት አንፃር የወደመው ቤተ ክርስቲያን በቅርብ ተገንብቶ እንደሚጠናቀቅ ያሳያል ብለዋል።መልሰን የማንገነባውና ድጋሚ የማናገኘው በህይወት ያጣነው ቅዱሱን ልጃችንን ነው በማለት ነፍሱን ከቅዱሳን እግር ስር እንዲያሳርፈው ተማፅነዋል። አያይዘውም መሰራት ያለበት ህንፃ ቤተክርስቲያን ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር ህንፃ የሆነው የሰው ልጅ ላይ ጭምር ነው።ስለዚህ ከቤተክርስቲያኑ ሥራ በተጓዳኝ ጠንካራ ጉባኤ ቤት ማቋቋምንም የፕሮጀክቱ አካል እንዲሆን አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመቀጠልም ታቦተ ህጉን አስገብተን አጠር ያለ የገቢ ማሰባሰብ መርሀ ግብር ተከናውኗል።
በመርሀ ግብሩም አባታችን ለሥራ ጉዳይ ወደጀርመን ተንቀሳቅሰው በነበረበት ጊዜ የመንፈስ ልጆቻቸውን ጠይቀው አሰባስበው የመጡት 100,000.00 ከእኔ ታገኛላችሁ ብለዋል ህዝበ ምእመኑም እንዳቅሙ ድጋፍ በማድረግ በእለቱ ጥሬ ብር 180,542.50 የተሰባሰበ ሲሆን በእህልም ከፍተኛ ገቢ ማሰባሰብ ተችሏል።
ያሰባሰብነው አጠቃላይ ጥሬ ብር 4,500,000.00 ተሻግሯል በቅርብ 5,000,000.00 እንደምንገባ ተስፋ አለኝ።
125 views05:49