2022-07-14 23:28:14
እኔን ብቻ ስሙኝ
*
ብዙሀኑ "እኔን ብቻ ስሙኝ" በሚሉበት በዚህ ጊዜ አባቱ "እርሱን ስሙት" ያለለትን ኢየሱስን ብቻ ስሙት!!
የክርስቶስ ልብ ያለህ አንተ ሆይ ሊኮንን የጸደቀ ማንም የለም!!
ከመናገርህ በፊት ኢየሱስ ቢሆን ምን ይናገራል በል!!
ከመጻፍህ በፊት ኢየሱስ ቢሆን ምን ይጽፋል በል!!
ከማድረግህ በፊት ኢየሱስ ቢሆን ምን ያደርጋል በል!!
ወዳጄ፦
አንተ እንደሞትክ ክርስቶስ በአንተ ሕያው ሆኖ እንደሚኖር ታውቃለህ?
❝ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ #እኔም_አሁን_ሕያው_ሆኜ_አልኖርም_ክርስቶስ_ግን_በእኔ_ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።❞
—ገላትያ 2: 20
አንተ ሞተህ ክርስቶስ ሕያው እንደሆነ ሲገባህ ሰደቡኝ ብለህ አጸፋ አትመልስም፡፡ #ክርስቶስ_አይሳደብማ!!
አንተ ሞተህ ክርስቶስ ሕያው እንደሆነ ሲገባህ ወንድምህ ላይ አትሳለቅም፡፡ #ክርስቶስ_አይሳለቅማ!!
አንተ ሞተህ ክርስቶስ ሕያው እንደሆነ ሲገባህ ጥግ ይዘህ አታፌዝም፡፡ #ክርስቶስ_አያፌዝማ!!
አንተ ሞተህ ክርስቶስ ሕያው እንደሆነ ሲገባህ ወንድምህን አትኮንንም!! #ክርስቶስ_አይኮንንማ!!
አንተ ሞተህ ክርስቶስ ሕያው እንደሆነ ሲገባህ ወንድምህን አታዋርድም፡፡ #ክርስቶስ_አያዋርድማ!!
አንተ ሞተህ ክርስቶስ ሕያው እንደሆነ ሲገባህ ወንድምህን ስታማ አትውልም፡፡ #ክርስቶስ_ሲያማ_አይውልማ!!
አንተ ሞተህ ክርስቶስ ሕያው እንደሆነ ሲገባህ በወንድምህ ላይ አታላግጥም፡፡ #ክርስቶስ_አያላግጥማ!!
ወዳጄ፦
ያጠፋውን መገሠጽ ያላወቀውን ደግሞ ማስተማር ትፈልጋለህ? እንግዲያውስ ክርስቶስን ስበክ!!
መጽሐፍ እንደሚል..........
❝እኛም በክርስቶስ ፍጹም የሚሆን ሰውን ሁሉ እናቀርብ ዘንድ #ሰውን_ሁሉ_እየገሠጽን_ሰውንም_ሁሉ_በጥበብ_ሁሉ_እያስተማርን_የምንሰብከው_እርሱ_ነው፤❞
—ቆላስይስ 1: 28
ማንም የሳተ ቢኖር አበሳጭተህ አትመልሰውም፤ አናደህ አታቃናውም!!
የሰው ቁጣ ትርፉ ለኢየሱስ ወግኖ የኢየሱስ ማደሪያ ላይ መሳለቅ ብቻ ነው!!
❝የሰው ቍጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ አይሠራምና።❞ —ያዕቆብ 1: 20
እኔ ማለት ካልቆመ መበሻሸቅ አይቆምም፤ መበሻሸቅ ካልቆመ እርሱ ማለት አይኖርም፤ እርሱ ማለት ከሌለ እኔ ማለት አይቆምም!!
እርሱን ስሙት!!
#ሄኖክ_አሸብር
167 viewsMercy Mekete, 20:28