ለሁላችንም ጥቆማ..... ቆም ብለን እንየውማ!! ❶]> ስማ ጀግናው ....ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም ። ሰዎች ስለደገፉህም የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን ፤ ምናልባት ዛሬ የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና አስተውል ተጠንቀቅ አትዝረክረክ ። ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ ዘመዳቸው ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ ንግግርህን ድንበር አታሳጣው በመረጃ ተመጠን ቆፍጠን በል ። እውነትንም በደጋፊ ብዛት እንዳትመዝናት ተጠንቀቅ!! ❷]>ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር ፤ ያን ስልህ የምትኖርበት ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና ስታከብርላቸው ነው ። ❸]>ልጅነት የለሰለሰ መሬት ፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን ፣ ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል ። በየ ሔድክበት ፊትና የማያጣህ መርህ አልባ አቋመ-ተልባ አትሁን ወንድ ወንድ ሽተት .... ........ሰለፍይነት ማለት ወንድነት እንጅ ወዳገረድነት አይደለም። ❝ወላሒ ልብ በል❞ ➺በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ ። http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi 2.9K viewsedited 14:28