በሱዳን ጋብ ብሎ የነበረው ጦርነት ማገርሸቱ ተሰማ
ንሥር ብሮድካስት
ሰኔ 5/2015
ውጊያው የቀጠለው ተፋላሚዎቹ ቀደም ሲል የደረሱት የ24 ሰዓታት የተኩስ አቁም ጊዜው ካበቃ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡
የ24 ሰዓታቱ የተኩስ አቁም ከእስካሁኖቹ በተሻለ ተከባሪ ነበረ ተብሏል፡፡
ቀዳሚዎቹ የተኩስ አቁሞች ተደጋጋሚ መጣስ ያጋጠማቸው ሲሆን ተፋላሚዎቹን በአንተ ነህ አንተ ነህ ሲያካሰሱ ሰንብተዋል፡፡
ትናንት የተኩስ አቁሙ እገዳ ውጊያ ተቀስቅሶባቸዋል ከተባሉት ስፍራዎች መካከል መዲናዋ ካርቱም እና ኦርዱርማን ይገኙበታል ተብሏል፡፡
2 ወራት ባስቆጠረው ጦርነት የተነሳ ሱዳንን ወደ ሕዝባዊ አስተዳደር ለማሸጋገር ተጀምሮ የነበረው ሂደት ተሰናካክሎ እንደቀረ ዘገባው አስታውሷል፡፡
=======================
ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት
YouTube 1: https://youtube.com/@nisirmedia2
YouTube 2: https://youtube.com/@nisir
FaceBook Page 1 : https://www.facebook.com/Nisirbroadcast
FaceBook Page 2: https://www.facebook.com/Nisirmereja
Telegram: https://t.me/nisirbroadcasting
Website: https://nisirbroadcasting.com
ንሥር ብሮድካስትን በወዳጅነት ይከታተሉን።