በርካታ ደህንነቶች በአማራ ክልል እንዲሰማሩ መመሪያ ወርዷል ንሥር ብሮድካስት ሰኔ 3/2015 ከዚህ በፊት በርካታ ቁጥር ያላቸው ደህንነቶች መግባታቸው ሲነገር ቆይቷል። አሁንም የአብይ አህመድ አገዛዝ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ አማርኛ ተናጋሪ ደህንነቶችን ወደ አማራ ክልል በተለይ ደግሞ ወደ ሰሜን ወሎ እና ሰሜን ጎንደር ለማሰማራት የደሞዝ እና የጥቅማጥቅም እንዲሁም በአማራ ስም በአማራ መታወቂያ ተዘጋጅቶላቸው የተልዕኮ ስልጠናቸውን ጨርሰዋል። ከአሁን በፊት የመደባቸው ደህንነቶች ከፊሎቹ የህዝቡን ጥያቄ በመጋራት ከፊሎቹ በመፍራት ከፊሎቹ ከህዝቡ ጋር በመላመዳቸው በታሰበው ልክ ለፋሺስቱ እንቅስቃሴ በታሰበው ልክ ስላልሆነ ይሄን በመገምገም አትታመኑም ዞር በሉ ተብለው የነበሩ የትግራይ ተወላጅ አማርኛ ተናጋሪ ከያሉበት ተጠርተው ኢ- መደበኛ በሆነ መንገድ ስምሪት ተሰጥቷቸዋል። እነሱም በከፍተኛ ወኔ ተልዕኮውን ተቀብለዋል"። ስለሆነም በአማራ ክልል በተለይ ደግሞ በተጠቀሱት ሰሜን ወሎ እና ጎንደር ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል ተብሏል። ወቅታዊ ፤ ትኩስ እና የተሟላ መረጃዎችን ለማግኘት Youtube: https://www.youtube.com/@nisir/videos FaceBook Page 1 : https://www.facebook.com/Nisirbroadcast FaceBook Page 2: https://www.facebook.com/Nisirmereja Telegram: https://t.me/nisirbroadcasting Website: https://nisirbroadcasting.com Twitter: https://twitter.com/NISIRInternati1 Instagram: https://www.instagram.com/nisirbroadcast/ ንሥር ብሮድካስትን በወዳጅነት ይከታተሉን። 2.3K views10:55