Get Mystery Box with random crypto!

የግእዝ ቋንቋ ትምህርት ስልጠና ለጀማሪዎች ለሁለት ወር በዚህ ዙር ላይም #20 ተማሪዎች ብቻ | ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ

የግእዝ ቋንቋ ትምህርት ስልጠና ለጀማሪዎች ለሁለት ወር

በዚህ ዙር ላይም #20 ተማሪዎች ብቻ ስለምንመዘግብ ቀድመው ይመዝገቡ

1. የስልጠናው ጥቂት ማብራሪያ
የትምህርቱ ዋና ዓላማ
→ የግእዝ ቋንቋን ተምረው ለማያውቁ ሰዎች ከመጀመሪያው አስጀምሮ ማሳወቅ እና ቋንቋውንም መደበኛ በሆነ መልኩ ከፊደላት አመጣጥ እስከ ግስ መገሰስ ለመማር የሚፈልጉትን አነሣሥቶ ጥንታዊ የሆነ ቋንቋችንን ለዘመኑ ትውልድ በሚመቸው በዘመናዊና ቀላል በሆነ የተመቻቸ አቀራረብ ማስተማር ነው። የተዘጋጀውም በሀገር ውስጥና በውጭም ለሚገኙ ወገኖቻችን ቋንቋውን ለማወቅ ፍላጎት ኖሯቸው ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች የመማር ዕድል ሳያገኙ ለቀሩ ጀመሪ ሰዎች ነው።
የትምህርቱ አሰጣጥ
→ ኮርሱ መሠረታዊ የሆኑ ትምህርቶች የያዘ ሲሆን በ4 ምዕራፎች ተከፋፍለው ይሰጣሉ። የትምህርት ጊዜያት ሰኞ እና ሀሙስ ሲሆን ከንጋቱ 1:3ዐ ሰዓት ላይ ትምህርቶች በየግላችሁ ይላክላችኋል።
ስለዚህም የዕለቱ በሚመችዎት ማንኛውም ሰዓት ላይ ገብተው መከታተል ይችላሉ።
→ ትምህርቶች የሚሰጡባቸው መንገዶች በጽሑፍ(pdf) ፣ በድምፅ(voice record) ሲሆን አጠቃላይ ዘመኑን በዋጀ መልኩ ይሰጣል ማለት ነው።

→ ውይይቶች፣ መልመጃዎች፣ የቤት ሥራዎች እንዲሁም የምዘና ፈተናዎች ይኖራሉ።

ትምህርቱን ላጠናቀቁ ተማሪዎችም የማጠናቀቂያ Certificate (የምስክር ወረቀት) ይሰጣል።

በስልጠናውም ፍጻሜ ከ70 በላይ የግእዝ መማርያ መጽሐፍት በPDF ይደርሶታል።

ለሁለት ወር የመማሪያ ክፍያ 250BIRR(የኢትዮጵያ ብር) ነው።

ለመመዝገብ ከፈለጉ @asrategabriel ላይ ያናግሩን
ለበለጠ መረጃ 0914946589
ላይ ዘወትር በስራ ሰዓት ብቻ ይደውሉ

ሰብሕዎ የልሳነ ግእዝ ማሰልጠኛ ተቋም