Get Mystery Box with random crypto!

በቡስካ ኢትዮጵያ የሚገኘው የአቡነ ሙሴ ጸሊም ገዳም ገድል እና ጉብኝት አንድ አምላክ በሆኑ በአብ | ንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ

በቡስካ ኢትዮጵያ የሚገኘው የአቡነ ሙሴ ጸሊም ገዳም ገድል እና ጉብኝት

አንድ አምላክ በሆኑ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኢትዮጵያዊ ጻድቅ የአባታችን የአቡነ ሙሴ ጸሊም ገድል ትሰሙ ዘንድ የመጣችሁ የቤተከርስቲያን ልጆች የሆናችሁ ወንዶችና ሴቶች በሙሉ ፈጽማችሁ በእዝነ ልቦናችሁ ስሙ አድምጡም ::
አባታችን የስሙን ትርጉም ብንመለከት ጸሊም ማለት ጨለማ ጥቁር ማለት ሲሆን ሙሴ ጸሊም መልኩ እጅግ ጥቁር የሆነ ጨለማን የሚመስል ፊት ያለው በትውልዱ ኢትዮጵያው ሲሆን አስቀድሞ በውንብድና ኑሮ ሕይወቱን ይገፋ ነበር፡፡ ሙሴ ጸሊም ከቅዱስ መቃርስ ጋር ከመገናኘቱ በፊት በፀሐይ የሚያመልኩ ጌቶች ያሉትና እርሱ ራሱም በባርነት የሚኖር በፀሐይ የሚያመልክ በነፍሰ ገዳይነቱ የታወቀና የሌቦች ሁሉ አለቃ የከፉ ምግባር ሁሉ ፈጻሚ ነበር:: ማንም በፊቱ ሊቀርብና ሊቋቋመውም አይችልም ነበር ሲበላና ሲጠጣም እንዲሁ ከልክ በላይ ነበር::
አንድ ቀን ራሱን ወደ ሰማይ ቀና በማድረግ ወደ ፀሐይዋ እያየ ፀሐይ ሆይ አንቺ አምላኬ እግዚአብሔር ከሆንሽ ራስሽን ግለጭልኝ ይል ነበር ከፀሐይ ምንም መልስ ሲያጣ አምላክ የኛ ጌቶች ናቸው በልተው ጠጥተው ከጥላ አርፈው የሚውሉ ፀሐይ ግን ሲመሽ ትጠፋለች ለጨለማ ቦታዋን ለቃ ሌሊት አትታይም ጠዋትም ትወጣለች ስትሄድ ትውላለች በማለት ለጓደኞቹ ነገራቸው እነሱም በዚህ በግብፅ በረሃ ውስጥ ገዳም አለ ወደዚያ ግባ አሉት እርሱም አቤቱ እኔ የማላውቅህ ጌታ እንዳውቅህ እርዳኝ አለ ወዲያውም አንድ ድምፅ ወደርሱ መጣ...ሙሉውን በቪዲዮ ለማግኘት

ሙሉውን የገድል እና ጉብኝት ቪድዮ ከታች ባለው ሊንክ መመልከት ትችላላችሁ