Get Mystery Box with random crypto!

ገፅ _ማህደር

የቴሌግራም ቻናል አርማ niahadu — ገፅ _ማህደር
የቴሌግራም ቻናል አርማ niahadu — ገፅ _ማህደር
የሰርጥ አድራሻ: @niahadu
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 132

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-10-18 14:55:49 ክፍል 5 ተለቀቀ



97 viewsTIGSTU AMBAW, 11:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-18 09:49:40 #በስብዕና ዙሪያ ምሁራኖች ምን ይላሉ?#አልማዝ ሳይሞረድ እንደማያንፀባርቅ ሁሉ ስብዕናም አለመከራ ቦግ አይልም::ይባላል!!
#ጊዜህን በምታገኘዉ ፍሬ ሳይሆን በምትዘራዉ ፍሬ ለካዉ በማንኛዉም ሁኔታ ዉስጥ ብትሆን መልካምነትን ዝራ!!
#በሰዉ ፊት የመናገር ክህሎትህ እየዳበረ በመጣ ቁጥር በራስ የመተማመን ፍጥነትህም በዚያዉ ልክ ይዳብራል!!
#እንዳያጋጥመን ከመስጋት ገጥመነው ብናሸንፈዉ የተሻለ ነዉ ይባላል!!
ፈታ ያለ ቀን ይሁንላችሁ ምርጦቼ
104 viewsTIGSTU AMBAW, 06:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-18 06:15:29 ይቅርታ ከመጠየቃችን በፊት ይቅርታ ለሚጠይቁ እና እነሱን ከማብራራታችን በፊት የእኛን ሁኔታ የሚያደንቁ እና...... የህይወት ጉድለቶቻችን ቢኖሩንም የሚወዱንን ጓደኞቻችንን አናጣም ግን ጓደኛ ማን እንደሆነ እንማራለን
ፈታ ያለ ቀን ተመኘሁ
85 viewsTIGSTU AMBAW, 03:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-17 10:16:47 ስትከፋ ወደ አምላክ ስትደሰት ወደ አለም አትሂድ::ታሞ ሲነሳ አምላኩን የረሳ አትሁን::
-
ለአለም ቁራጭ ደስታ ስትል የአምላክን ዘለዓለማዊ ደስታ አትርሳ::ባንተ ውስጥ ያለውን አምላክ ስታገኝ የአለምን ርካሽነት ታገኛለህ::
-
እስቲ ወደ ልቡ ቅረብ : ወደ ሀሴት ምንጭ ያቀርብሃል::መንፈስህም በደስታ የሰከረ ነበልባል ይሆናል::ችግሮችህ ሁሉ ተማግደው ይነዳሉ::ልክ እንደ አመድ ደቄት ይሆናሉ::
-
ወደ አምላክህ ቀርብህ "ይሄንና ያን አድርግልኝ!" እያልክ ብቻ አትነዝንዘው::ዝም ብለህ ከእርሱ ጋር ብቻ ሁን::ተጣበቀውና መንፈሱን ቅመሰው::እርሱ የሚይስፈልግህን ሁሉ ያውቃል::በልብህም እርሱን ምን መጠየቅ እንዳለብህ ሀሳብን ያፈልቃል::የምታሳካበትን መንገድም በራሱ ያመጣል::
-
መጀምርያ ለምን ችግር ውስጥ እንደወደክ ታውቃለህ? መጀመርያ እርሱን መስማት ስለተሳነህ ነው::አምላክህ ምን እያለህ ነው? በትዳርህ? በገንዘብህ? በትምህርትህ? በአገርህ? አና በአለም ዙርያ ያንተ አምላክ ምን እያለህ እንደሆነ ታውቃለህ? ጫጫታውን ፀጥ አሰኝና የሚልህን ስማው::በአለምም ሆነ ከአለምም ወዲያ ባለው ህይወት አሸናፊ የምትሆንበትን ሚስጢር ይሰጥሃል::ስማው!!
-
#መልካም_ዕለተ_ሰንበት!
1.2K viewsTIGSTU AMBAW, 07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-17 07:58:58 የሕይወት ዋጋው ስንት ነው

ከዕለታት ባንዱ ቀን አንድ ታዳጊ አባቱን፦ “የሕይወት ዋጋው ስንት ነው?” ሲል ጠየቀው። አባትም መልስ በመስጠት ፈንታ ልጁን እንዲህ ሲል አዘዘው፦ “እንካ ይህንን የድንጋይ ቁራጭ፤ ወደ ገበያ ውሰደው። ሰዎችም ዋጋውን ከጠየቁህ በጣቶችህ ሁለት ቁጥርን ብቻ አሳያቸው እንጂ ምንም አትናገር!” አለው።

ልጁም ድንጋዩን ወስዶ፤ በገበያ መሃል ቆመ። አንዲት ሴትም መጣ፦ “ይህ ድንጋይ ዋጋው ስንት ነው? ብትሸጥልኝ ወስጄ ግቢዬ ውስጥ አስቀምጠዋለሁ።” አለችው። ልጁም እንደታዘዘው ምንም ሳይናገር ሁለት ጣቶቹን አሳያት። እሷም አለች “ሁለት ብር? እወስደዋለሁ!!!”

ልጁም ወደ ቤቱ ተመለሰ። በገበያ ያጋጠመውንም ለአባቱ ነገረው። አባትየውም፦ “አሁን ደግሞ ድንጋዩን ይዘህ ወደ ሙዚየም ሂድ። ዋጋውን ሲጠይቁህም ሁለት ጣቶችህን አሳይ።” አለው።

ልጁም ወደ ሙዚየም ሄደ። ገዢም መጥቶ ዋጋ በጠየቀው ጊዜ ሁለት ጣቶቹን አሳየው። ገዢውም “ሁለት መቶ ብር? እወስደዋለሁ!” አለው። ልጁም በድንጋጤ ወደ ቤቱ ተመለሰ። ያጋጠመውንም ነገር ለአባቱ ነገረው።

አባትየውም ተናገረ፦ “አሁን ደግሞ በመጨረሻ ድንጋዩን ይዘህ ወደ የከበሩ ማዕድናት መሸጫ ሂድ። ለባለቤቱም አሳየው!” አለው።

ልጁም ሄዶ ለሱቁ ባለቤት አሳየው። የሱቁ ባለቤት በመገረም፦ “ይህ እኮ ዓለም ላይ እጅግ ውድ ከሆኑ የከበሩ ድንጋዮች አንዱ ነው።” አለ።

“ከየት አገኘኸው? ስንትስ ትሸጠዋለህ?” ሲል ጠየቀው። ልጁም ምንም ሳይናገር ሁለት ጣቶቹን አሳየ። የሱቁም ባለቤት፦ “ይህንን ድንጋይ በሁለት መቶ ሺህ ብር እወስደዋለሁ።”

ልጁም በመገረም እየሮጠ ወደ ቤቱ ተመልሶ ያጋጠመውን ለአባቱ ነገረው። አባትየውም፦ “ልጄ አሁን የሕይወትህ ዋጋ ተገልጦልሃል?!” አለው።

ቁምነገር!

አየህ የመጣህበት ቦታ፣ ዘርህ፣ ሃይማኖትህ፣ የቤተሰቦችህ ሃብት፣ የተወለድክበት ቦታ ልዩነት አይፈጥርም። ዋናው ራስህን የምታስቀምጥበት ቦታ፣ ራስህን የምታገኝበት የሰዎች ስብስብ ነው። ልዩነቱ ያለው ራስህን ለመሸከም በምትመርጥበት መንገድ ነው። ሕይወትህን ሙሉ የሁለት ብር ድንጋይ ዋጋ ስትሰጠው ኖረህ ይሆናል።

ሕይወትህን ሙሉ የኖርከው ዋጋህ ሁለት ብር ብቻ እንደሆነ በሚያስቡ ሰዎች ተከበህ ይሆናል። ነገር ግን እያንዳንዱ ሰው ውድ የሆነ የከበረ ድንጋይ በውስጡ ይዟል። ልዩነቱም ያለው ውስጣችን ያለውን የከበረ ድንጋይ አይተው ዋጋ በሚሰጡን ሰዎች መሃል መገኘትን ስንመርጥ ነው።

ራሳችንን በገበያ ወይም በከበሩ ማዕድናት ሱቅ የማስቀመጥ ምርጫው አለን። በሌሎች ሰዎች ውስጥ ያለውንም ውድ ዋጋ ለማየት ምርጫው የኛው ነው። ሌሎች ሰዎችም የከበረ ዋጋቸውን እንዲረዱ ማድረግ እንችላለን። አብረህ የምትውላቸውን ሰዎች በጥንቃቄ ምረጥ። ይህ በሕይወትህ ልዩነትን ይፈጥራልና!

(ሻውን ቡንደናሂራን ከተረከው፣ የተተረጎመ)

Hiju@...
85 viewsTIGSTU AMBAW, 04:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-15 09:52:46 አንድ ሴት መንገድ ላይ እየሄደች አንድ ልጅ ከኋላዋ ሲሮጥ ሰምታ ዞር አለች "ባንቺ ውስጥ ሴትነት ውበት አለ ወደድኩሽም" አላት

ፈገግ ብላ "ከኔ በላይ ቆንጆ እና በሴትነቷም ከኔ የተሻለች ጓደኛዬ ከኋላክ አለች " ስትለው ዞሮ ፈለገ ግን ምንም ሴት አላየም" የታለች?" አላት እሷም #ፈገግ ብላ"ወደኸኝ ቢሆን ኖሮ ሌላ ባልፈለክ ነበር " ብላ መንገዷን ቀጠለች።

በአንድ ምክንያት የሚወድህ ሰው በሌላ ምክንያት ይለይሀል ለምን እንደሚወድህ የማያውቀው ግን ሁሌም ቢሆን ይወድሀል.....

ሰናይ ቀን ተመኘው
389 viewsTIGSTU AMBAW, 06:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-14 06:59:26 ይቅርታ ከመጠየቃችን በፊት ይቅርታ ለሚጠይቁ እና እነሱን ከማብራራታችን በፊት የእኛን ሁኔታ የሚያደንቁ እና...... የህይወት ጉድለቶቻችን ቢኖሩንም የሚወዱንን ጓደኞቻችንን አናጣም ግን ጓደኛ ማን እንደሆነ እንማራለን
ፈታ ያለ ቀን ተመኘሁ
1.6K viewsTIGSTU AMBAW, 03:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-13 13:55:04 አንድ ህፃን ልጅ ለመራመድ ቢያንስ 50 ጊዜ ይወድቃል::ሲወድቅ ግን ሰዎች ያበረታቱታል እንጂ በመውደቁ አይተቹትም::ለዛ ነው ሁሉም ህፃን መራመድን የቻለው::
-
ስናድግ ግን ይህ ታሪክ ይለወጣል አዲስ ነገር ሞክረን ስንሳሳት ሰው ሁሉ እንደ ልጅነታችን ከማበረታታት ይልቅ መውቀስ እና መተቸትን ያጎርፋል::ለዛም ነው ፈሪ እንጂ አድራጊ ያልሆንነው::እንደ ልጅነታችን እንሁን::
-
ሙሉውን በእኔ ዩቱብ ተከታተሉ!
86 viewsTIGSTU AMBAW, 10:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-13 08:29:52 #የአስተሳሰብህ_እስረኛ_አትሁን

የታሰርክበት ገመድ ጥንካሬ አለማወቅህ ሁሌም እስረኛ እንድትሆን
አድርጎሀል።
የታሰርከው ገመዱ ጠንካራ ስለሆነ ሳይሆን ገመዱ ጠንካራ ነው ብለህ
ስላሰብክ ነው።
ለመበጠስ ወይም ለመጎተት ሞክረህ አታውቅማ ብትሞክረው ገመዱን
ብቻ ሳይሆን ገመዱ የታሰረበትን ላንተ ትልቅና ጠንካራ መስሎ የታየህን
የፕላስቲክ ወንበር እንደፈለክ ባደረከው ነበር!! ዳሩ ግን አልሞከርከውም!!
ትልቁም ችግር አለመሞከርህ ነው።አስሮ ያስቀመጠህ የጠላትህ ጥንካሬ
ሳይሆን ያንተው የገዛ ድክመትህ ነው።
ከታሰርክበት ወንበር ሚሊዎን ጊዜ የሚበልጥ አቅምና ጉልበት እንዳለህ
አታውቅም???
አንዴ እግርህን ብትጥልበት ብትንትኑ እንደሚወጣ አታውቅምን??
መቼም መታሰሩን ፈልገህው አይመስለኝም?, ታድያ ምን
ትጠብቃለህ ??
ለራስህ አዳኙም ገዳዪም እራስው ነህ ካለመቻል ወደ መቻል ተለማመድ ያኔ ሁሉም ይፈታል።


ምርጥ ቀን ተመኘሁ
82 viewsTIGSTU AMBAW, 05:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-12 10:16:23 እንዴት አደራችሁ

አጭር አስተማሪ ታሪክ

ለምጣዱ ሲባል...!

አዲት ሴትዮ ጓዳቸው ውስጥ እየተንጎዳጎዱ ድንገት አዲት አይጥ ምጣዳቸው ላይ ትወጣለች ወንድ ልጃቸው እንጨት ያነሳና አይጧን ለመምታት ሊሰነዝር ሲል ሴትዬዋ አስቆሙት " ልጄ አይጧን ስትመታ እንጀራ ማብሰያችንን ምጣዱን ሰበርከው ማለት ነው ስለዚህ ግድ የለም ለምጣዱ ሲባል አይጧን ዝም እንበላት" አሉት ይባላል።

ሁሌም ለምንፈልገው ነገር ስንል ብዙ ነገሮች መታገስ እንዳለብን፣

ከመወሰናችን በፊት ማስተዋል እንዳለብን ከታሪኩ እንረዳለን።

መልካም ቀን ይሁንልን
642 viewsTIGSTU AMBAW, 07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ