Get Mystery Box with random crypto!

' እባክችሁ መፍትሄ ስጡን ፤ ጊዜው ያለ ትምህርት እየሄደብን ነው ' - ተማሪዎች በአማራ ክልል | ትምህርት ሚኒስቴር

" እባክችሁ መፍትሄ ስጡን ፤ ጊዜው ያለ ትምህርት እየሄደብን ነው " - ተማሪዎች

በአማራ ክልል ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የሚማሩ ተማሪዎች እስካሁን ወደ ትምህርት እንዳልተመለሱ በመግለፅ ትምህርት ሚኒስቴር መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጥሪ አቀረቡ።

መልዕክታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩ ተማሪዎች እስካሁን የሚማሩባቸው ግቢዎች እንዳልጠሯቸው በማመልከት ያለ ትምህርት መቀመጣቸውን ገልጸዋል።

በእነሱ እድሜና ተመሳሳይ የትምህርት ደረጃ የሚገኙ በሌሎች ክልሎች በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ጓደኞቻቸው ትምህርታቸውን ለመጀመር ወደ ሚማሩበት ተቋም ከበርካታ ቀናት በፊት መግባታቸውን እነሱ ግን እስካሁን መቼ እንኳን እንደሚጠሩ እንደማያውቁ በመግለፅ ትምህርት ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ መፍትሄ ቢሰጥ ብለዋል።

ተማሪዎቹ ከእኩዮቻቸው ወደ ኃላ እየቀሩ መሆኑን አመልክተው ይህም የሚያሳድረው ጫና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የፊልድ ምርጫ ካደረጉ በኃላ ወደቤት ተመልሰው ከወራት በላይ ያለትምህርት መቀመጣቸውን አመልክተዋል።

" ትምህርት ሚኒስቴር ስለኛ ጉዳይ ችላ ማለት የለበትም " ሲሉ ያሳስቡት ተማሪዎቹ የትግራይ ተማሪዎች አይነት ዕጣ ፋንታ እንዳይደርሰን ከወዲሁ አፋጣኝ መፍትሄ ይፈለግልን ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

በሌላ በኩል ፤ በአማራ ክልል ባለው ተለዋዋጭ የሆነ የፀጥታ ሁኔታ ከአማራ ክልል ወደ ተለያዩ ክልሎች ወደሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ሄደው መማር ያልቻሉ ተማሪዎች ስለመኖራቸው ለማወቅ ተችሏል።

ተማሪዎቹ በፀጥታ ሁኔታ ምክንያት ለመሄድ መንገዶች ፈታኝ እንደሆነባቸው አመልክተዋል።

አቅም ያላቸው በአየር ትራንስፖርት ፤ አንፃራዊ ሰላም ያለባቸው ቦታዎች የሚኖሩ በብዙ ብር በየብስ ትራንስፖርት ወደ ሚማሩበት ተቋም መግባታቸውን ነገር ግን የፀጥታና ደህንነት ሁኔታው ባልተሟላባቸው በተለይ ጎጃም አካባቢዎች ያሉ ተማሪዎች ወደ ትምህርት መመለስ እንዳልቻሉ የደረሱን መልዕክቶች ያስረዳሉ።

ያለው የትራንስፖርት ዋጋም ውድ በመሆኑና መንገዶችም ስለሚያሰጉ እንደ " ቀይ መስቀል " አይነት ተቋማት እስካሁን ወደ ተቋማቸው ያልገቡ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ተቋማቸው የሚወስዱበት መፍትሄ እንዲፈለግ ጠይቀዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ተወካይ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑን ለቪኦኤ ሬድዮ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

ዶ/ር ሰለሞን ፤ የደህንነት ችግር ካለባቸው አካባቢዎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ወደ ተቋማቸው የመመለሱ ስራ የሚሰራው ከወታደራዊ ኮማንድ ፖስት ጋር በመተባበር ነው ብለዋል።

" አሁን ባለው ሁኔታና ካለው የፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ዩኒቨርሲቲዎች በሴኔት ተማሪዎችን የሚቀበሉበትን ቀን እየወሰኑ ተማሪዎችን እየጠሩ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው። ይሄ ደግሞ እየተሰራ ያለው በዋናነት የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች በአካባቢው ከሚገኙ የኮማንድ ፖስት አካላት ጋር በቅርብ እየተወያዩ ለተማሪዎች ካለው Safety እና Security አኳያ እየተገመገመ እየተሰራ እንደሆነ እናውቃለን " ብለዋል።

" እንደ ትምህርት ሚኒስቴርም ያለው concern ትክክለኛ ስለሆነ በቅርብ እየተከታተልን ነው። የሚፈለገው የድጋፍ እና ክትትል ስራ እየሰራን ነው። እስካሁን የጎላ ችግር አልቀረበም በኛ በኩል ቀጣይ የሚነሱ ችግሮች ካሉ በዛው ካለው የፀጥታ አካላት ጋር በጋራ ሆነን እንሰራለን " ሲሉ ተናግረዋል።

@News_For_Student
@News_For_Student