Get Mystery Box with random crypto!

' ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ወደ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተዛውሮ መማር አይቻልም ' | ትምህርት ሚኒስቴር

" ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ወደ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተዛውሮ መማር አይቻልም " - ትምህርት ሚኒስቴር

የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ በ2015 ዓ/ም የሬሜዲያል ትምህርት ተከታትለው 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡ ተማሪዎች የፍሬሽማን ኮርስ እንዲማሩ መወሰኑን አስታውሷል።

በዚህም መሰረት ፦

- ከመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዛውሮ መማር እንደሚችሉ፤

- ከአንድ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ወደ ሌላ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተዛውሮ መማር እንደሚችሉ እና

- ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ወደ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተዛውሮ መማር የማይችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አስገንዝቧል።

ተማሪዎች ከአንድ ተቋም ወደ ሌላ ተቋም ሄደው መማር የሚፈልጉ ከሆነ መረጃቸው በአግባቡ ተደራጅቶ እንዲሰጣቸው ትምህርት ሚኒስቴር በፃፈው ደብዳቤ አሳስቧል።

(በሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተወካይ ተፅፎ ለተቋማት የተላከው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል)

@News_For_Student
@News_For_Student