2022-06-27 10:39:35
ታላቅ የክረምት ኮርስ ምዝገባ በደሴ
አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱሂ ወበረካቱህ
ዉድና የተከበራችሁ ወንድምና እህቶች እነሆ የ አል ኢህሳን መርከዝ ለሁለት ወር የሚቆይ ኢስላማዊ ኮርስ ለመስጠት ዝግጅቱን ያጠናቀቀ ሲሆን ካሁን ሰአት ጀምሮ እውቀት ፈላጊ የሆኑ ወንድምና እህቶች መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን ያሳዉቃል፡፡
መርከዙ ለሁለት ወር በራሱ ወጭ የሚያስተናግደው የተማሪዎች ብዛት 50 ሲሆን ከወንዶች 30 ከሴቶች ደግሞ 20 ብቻ ነው ስለሆነም ቦታው ሳይሞላ ፈጥናቹህ እንድትመዘገቡ ያሳዉቃል፡፡ በራሱ ወጭ ኮርሱን መከታተል የሚፈልግ በዬትኛዉም ሰዓት መመዝገብ ይችላል።
ማሳሰቢያ
1 መርከዙ በራሱ ወጭ(ምግብና ማደሪያ) 50 ሰወችን ብቻ የሚያስተናግድ ሲሆን ከ 50 በላይ ላሉ ተማሪዎች ወጫቸዉን ከሸፈኑ መርከዙ በነጻ መዝግቦ የሚያስተምር መሆኑን እንገልጻለን ፡፡
2 መርከዙ ለሁሉም ተማሪዎች ኮርሱን በነጻ የሚሰጥ ሲሆን ለመጀመሪያ መመዝገቢያ 500 ብር ያስከፍላል፡፡
3 እያንዳንዱ ተማሪ ወደመርከዙ በሚመጣ ሰአት የሌሊት ልብስ እና ፍራሽ ዪዞ መምጣት ዪጠበቅበታል፡፡
4 መርከዙ በራሱ ወጭ ለሚያስተምራቸው 50 ተማሪዎች ከ ሰኔ 20/10/14 እስከ ሰኔ 24/10/14 ባለው ሰአት ብቻ ምዝገባ የሚያካሂድ ሲሆን በራሳቸው ወጭ ለሚማሩ ተማሪዎች በየትኛዉም ሰአት መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
5 በመርከዙ ወጭ ለመማር የተመዘገቡ ተማሪዎች ከ ሃምሌ 1/11/14 እስከ ሐምሌ 5/11/14 ድረስ መግባት ዪጠበቅባቸዋል፡፡
6 ለኮርሱ ለመመዝገብ ማንኛዉም ተማሪ ቁራን በነዞር መጨረስ ዪጠበቅበታል፡፡
7 የምንቀበላችው የ ሴት ተማሪዎች መርከዙ ድረስ አምጥቶ ሃላፊነተቸዉን የሚወስድ መህረም ማምጣት ዪጠበቅባቸዋል፡፡
8 ማንኛዉም ተማሪ ወደ መርከዙ ሲመጣ ህጋዊ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅበታል።
አል ኢህሳን መድረሳ በደሴ
አድራሻ
ደሴ ከ ኬላ ከፍ ብሎ ኳስ ሜዳ አልታቤ ትምህርት ቤት አጠገብ
የመመዝገቢያ ፎርም
1 ሙሉስም___
2 ዕድሜ___
3 ፆታ___
4 ሃገር___
መመዝገቢያ
ከታች ያለዉን ሊንክ በመጫን መመዝገብ ትችላላቹህ
ለወንዶች
@TellTheTruth12
@Abumuaz9
@abureyyis
ለሴቶች
@R_muktar
@Bint_seid_ukht_nure
አል ኢህሳን መርከዝ የቴሌግራም ግሩፕ
t.me/AlihsanCharityAssociation
t.me/AlihsanCharityAssociation
107 views07:39