የመጀመሪያዎቹ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሠሩ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶች በአዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል። የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶቹ በበላይነህ ክንዴ ግሩፕ የተገጣጠሙ መሆናቸው ነው የተገለጸው፡፡ አውቶብሶቹን ወደ ሥራ ያስገባው በቅርቡ 20 በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሠሩ ሚኒባሶችን ወደ ሥራ ያስገባው የግሩፑ እህት ድርጂት ቬሎሲቲ ኤክስፕረስ ነው ተብሏል፡፡ ዛሬ ሥራ የጀመሩት አውቶብሶች መነሻቸው ቦሌ ሲሆን መዳረሻቸው ደግሞ በእስጢፋኖስ -4 ኪሎ- 6 ኪሎ ሽሮ ሜዳ መሆኑን የተቋሙ መረጃ ያመላክታል፡ 25.2K views16:46