2022-05-27 22:35:31
# በእስልምና ጥላቻ የጦዘው ጀርመናዊው ፖለቲከኛ...
እስልምናን እና አማኞቹን አጥብቆ የሚጠላው አክራሪ የፖለቲካ ዘውግ
አራማጁ፤ ተፅዕኖ ፈጣሪው ጀርመናዊ ፖለቲከኛ አርቱር ዋግነር በእንግዳነት
በታደመበት ሚዲያ ላይ ሁሉ እስልምናን ሳይዘልፍ፤ አማኞቹን ሳያብጠለጥል
ንግግሩን አሳርጎ እንደማያውቅ ብዙዎች ይናገራሉ...
በጀርመን ያቋቋመው (AFD) ፓርቲ በማሕበረሰቡ ዘንድ ቅቡልነት የተቸረው
በመሆኑ ያሻውን ለመዝለፍ፤ የፀዳውን ለማጉደፍ አጨብጫቢ እንጅ ለምን? እና
እንዴት? ብሎ የሚጠይቅ አለመኖሩ የእስልምና ጥላቻውን የበለጠ ማባባሱ
እንደ ምክንያት ይጠቀሳል...
አንድ ወቅት ላይ በሐገሪቱ ቴሌቪዢን ለደጋፊዎቹ የሚነግራቸው አንገብጋቢ
ጉዳይ እንዳለው በመግለፅ በጉጉት ለሚጠብቁት፤ ለፖለቲካው ማጣፈጫ
እስልምናን በማጠልሸቱ የሚጎመዡለት ደጋፊዎቹ በጉጉት እየጠበቁት ነው!
አርቱር ዋግነር ከበፊቱ በተለዬ ፈገግታ በቀጥታ ስርጭት እንግዳ ሆኖ ቀረበ!
ጋዜጠኛውም መልዕክቱን እንዲያስተላልፍ እድሉን ሰጠው...
ለእስልምና ባለው ጠላትነት 'Prominent' የሚታወቀው እውቁ ፖለቲከኛም
አለ:-"እኔ ሳላውቅ ከገደብ በላይ በምጠላው እስልምና የማይወላውል ፅኑ
መንገዴን ጀምሪያለሁ! እስከዛሬ እስልምናን በመጥፎ ሳነውር የነበረው በጭፍን
ነው፤ እውነታውን ከእኔ ፀያፍ ቃል በተቃራኒ ሆኖ በአስተምሕሮው ጥራዝ ውስጥ
አግኝቼዋለሁ! እናንተም ለማወቅ ሞክሩ!" በማለት! ዛሬስ እስልምናን ምን ብሎ
ሊሰድብልን ነው? ብለው በጉጉት ለሚጠብቁት ደጋፊዎቹ ዱብዳውን
አረዳቸው...
ጋዜጠኛውም :-"እንዴት ከመጠን በላይ ወደምጠላው'ና በጠላትነት ከፈረጅከው
እስልምና ልገባ ቻልክ " በማለት በግርምት ጠዬቀው...
አርቱር ዋግነርም:-" ለረጅም ዓመታት የፈጠረኝን አምላክ እና የፈጠረብኝን ዓላማ
ለማወቅ በጥረት የታከለው ጉገቴ እውነታውን ሊያመላክተኝ አልቻለም ነበር! ለካ
እውነታውን ጥላቻዬ ሸፍኖኝ ኖሯል፤ ሁሉንም ፈትሼ ለጥያቄዬ አመርቂ መልስ
ሳጣ በጭፍን የጠላሁትን እስልምና ለመፈተሽ ተገድጃለሁ! ነገር ግን
በእስልምና ውስጥ የጥያቄዬን ምላሽ ብቻ ሳይሆን የማላውቃቸውን እልፍ
አምላካዊ ተግሳፆችን ለተራበችው ነፍሴ ብርታት አድርጌ መግቤያቸዋለሁ!"
በማለት የመስለሙን ምክንያት አብራርቷል...
ወደ ተፈጥሯዊ እምነቱ እስልምና ከገባ ቡኃላ ስሙን 'አሕመድ' በማለት
መጠሪያው ያደረገው አርቱር ዋግነር በተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ ላይ ቤተ-ክርስቲያኗ
ያላትን አቋም በግልፅ በመቃዎም ግብረ ሰዶማዊነትን ከተለምዶ አስተሳሰብ እና
እምነት ጋር የሚጣረስ ያልተገራ ተግባር ነው! በማለት የጀርመንን ካሕናት
እየሞገተ እንደሆነ'ና ብዙዎችን እስልምናን በማስተማር ወደ ተፈጥሯዊ
እምነታቸው እየመለሰ እንደሚገኝም ተገልጿል። [Converts to islam
364 viewsOzil Ozil , 19:35