ዘካ የሌለባቸው ንብረቶች ~ ① ለንግድ ሳይሆን ለቤት ፍጆታ የተቀመጡ ንብረቶች (ሸቀጣ ሸቀጥ፣ ምግቦች፣ እህሎች፣ መገልገያ ቁሳቁስ፣ መገልገያ እንስሳት፣ ለሽያጭ ያልቀረቡ አልባሳት) ዘካ የለባቸውም። ② ለሽያጭ ሳይሆን ለኪራይ የተዘጋጁ ቤቶች፣ መኪናዎች፣ ማሽኖች፣ ወዘተ በራሳቸው ዘካ የለባቸውም። ዘካ የሚመለከታቸው ከኪራይ የተሰበሰበው ገንዘብ ለዘካ መጠን ደርሶ አመት ከሞላው ነው። ③ ከወርቅና ብር ውጭ ያሉ ማእድኖች (አልማዝ፣ ፕላቲነም፣ ውድ የሆኑ የድንጋይ አይነቶች፣ …) በራሳቸው ዘካ የለባቸውም። ለንግድ ከዋሉ ግን እንደማንኛውም የንግድ ሸቀጥ ዘካ ይመለከታቸዋል። ④ የህዝብ ማመላለሻና የጭነት መኪኖች በገቢያቸው እንጂ በራሳቸው ዘካ የለባቸውም። የሚያስገቡት ገቢ ለዘካ መጠን ከደረሰ በኋላ አመት ከሞላው የአጠቃላዩን 2•5% ዘካ ይወጣል። [መጅሙዑል ፈታዋ፣ ኢብኑ ባዝ: 14/181] [አልለጅነት አድዳኢማህ: 9/349] ⑥ ለሽያጭ ወይም ለአገልግሎት መሆን አለመሆኑን በቁርጥ ያልተወሰነበት ቤት ወይም መኪና ዘካ የለበትም። ⑦ ተበዳሪው ችግረኛ በመሆኑ ወይም የሚያጉላላ በመሆኑ ይመለሳል ተብሎ ተስፋ የማይጣልበት ብድር ዘካ አይወጣበትም። ማሳሰቢያ ----------- * ብድሩ ተመልሶ ድንገት እጅ ከገባና ለዘካ መጠን የደረሰ ከሆነ እጅ ከገባበት ጊዜ አንስቶ አመት ሲሞላው ዘካው ይወጣል። * ብድሩ ቢጠይቅ የሚያገኘው አይነት ከሆነ እጁ ባይገባም ዘካ ይመለከተዋል። * በጊዜ የተገደበ ብድር ከሆነ (ለምሳሌ የዛሬን አመት እከፍላለሁ ቢለው) ጊዜው እስከሚደርስ ዘካ አይመለከተውም። ወላሁ አዕለም። = ( Ibnu Munewor ፣ ሚያዚያ 21/2013) የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor 263 viewsumu abdul basit ደግ ልቦች ከውብ ፊቶች ይበልጣሉ ቁጥብ ሁኚ ውድ ትሆኛለሽ , 06:19