#የሰላምታ_ትሩፋትና #ሰላምታን_ማብዛት_ስለመታዘዙ #ክፍል_2 አላህ እንዲህ ብሏል፦ “በሰላምታ በተከበራችሁም ጊዜ ይበልጥ ባማረ (ሰላምታ) አክብሩ፤ ወይም (እርሷኑ) መልሷት፡፡” (አን ኒሳእ፡ 86) #ሐዲሥ 131 / 846 አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት ነቢዩ እንዲህ ብለዋል፦ “አላህ አደምን በፈጠረ ጊዜ ‘ለነዚያ _ለተቀመጡት መላእክት_ ሰላምታ አቅርብላቸው። ምላሻቸውንም በጥሞና ስማ። ያንተና የዝሪያዎችህ ሰላምታ ነውና’ አለው። ‘አስሰላሙ ዐለይኩም’ አላቸው። ‘አስሰላሙ ዐለይከ ወረሐመቱላሂ’ በማለት የሚል አክለው መለሱለት፡፡” (ቡኻሪና ሙስሊም) ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች 1/ “አስሰላሙ ዐለይኩም” የሚለው ቃል ኢስላማዊ የሰላምታ አቀራረብ ስልት ነው። አላህ ይህን ቃል አደምን ከፈጠረበት ዕለት አንስቶ ለባሮቹ ሰላምታ አድርጎታል። 2/ ሰላምታ ሲመልሱ በርከት አድርጎ መመለስ በላጭ መሆኑን ሐዲሡ ያሳያል። “አስሰላሙ ዐለይኩም” ላለ “ወዐለይኩሙ ሰላም ወረሕመቱላሂ ወበረካቱሁ” በማለት ማከል በላጭ ነው። 354 views 𝙯𝚞𝚣𝚞 ደግ ልቦች ከውብ ፊቶች ይበልጣሉ ቁጥብ ሁኚ ውድ ትሆኛለሽ , 19:33