Get Mystery Box with random crypto!

የትግራይ ክልል መንግስት መስሪያ ቤቶች፤ ለሰራተኞቻቸው ብድር እንዲሰጡ ተፈቀደላቸው በትግራይ ክ | Muktarovich Ousmanova

የትግራይ ክልል መንግስት መስሪያ ቤቶች፤ ለሰራተኞቻቸው ብድር እንዲሰጡ ተፈቀደላቸው

በትግራይ ክልል የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ እስከሚከፈላቸው ድረስ ከመስሪያ ቤቶቻቸው ብድር እንዲወስዱ ተፈቀደላቸው። የክልሉ መስሪያ ቤቶች ለሰራተኞቻቸው ማቅረብ የሚችሉት ከፍተኛ ብድር፤ አራት ሺህ ብር እንደሆነ ተገልጿል።

የትግራይ ክልል መንግስት ሰራተኞች የመከላከያ ሰራዊት ክልሉን ለቀቆ ከወጣበት ከሰኔ 2013 ዓ.ም አንስቶ፤ ላለፉት 21 ወራት ደመወዝ አልተከፈላቸውም። የፌደራል መንግስት እና ህወሓት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ባደረጉት ስምምነት መሰረት ሊቋቋም ይገባ የነበረው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ መንግስት እስካሁን ባለመቋቋሙ፤ የገንዘብ ሚኒስቴር ወደ ክልሉ ገንዘብ አለመላኩን ባለፈው ሳምንት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታውቆ ነበር።

እስካሁን በጀት ያልተለቀቀላቸው የክልሉ የመንግስት መስሪያ ቤቶች፤ በባንክ ሂሳባቸው ውስጥ ካለው ገንዘብ ውስጥ ለሰራተኞቻቸው ብድር ለመስጠት ጥያቄ ማቅረባቸውን እና ጥያቄያቸው ተቀባይነት ማግኘቱን የክልሉ የገንዘብ እና ፕላን ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አረጋዊ ገብረሚካኤል ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። ቢሮው በክልሉ ለሚገኙ ለሁሉም የዞን፣ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም መስሪያ ቤቶች ባለፈው ሳምንት ሐሙስ መጋቢት 7፤ 2015 በጻፈው ደብዳቤ፤ ብድር እንዲሰጡ መፍቀዱን ኃላፊው አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያን ኢንሳይደር