2022-07-26 19:36:05
ከጀናዛ ማጠቢያ ክፍል ቁ•3
የወጣቱን ጀናዛ ሳጥብ ባጋጠመኝ አስደንጋጭ ክስተት ምክንያት ወደራሴ ለመመለስ ረጅም ጊዜ ፈጅቶብኛል ። ጀናዛን ባየሁ ቁጥር መደንገጥና መሸበር ጀምሬያለሁ። ከስድስት አመት በፊት የተፈጠረ ታሪክ ነው።
ኑ ተከተሉኝ ታሪኩን ላውጋችሁ ለሚገሰፅ ሰው ትምህርት ነውና።
ወደ ጀናዛ ማጠቢያው ስፍራ ገባሁ በማጠቢያ እንጨት ላይ ተንጋሎ የተኛ ረጅም ቀይ ሩሑ ስትወጣ መልኩ ቢጫ የሆነ ሰው ይታየኛል። አብዱረህማን የተባለ ሊያግዘኝ ፈቃደኛ የሆነ ወጣት ከጎኔ አለ። ሲድርና ካፋርን አዘጋጀን ። የሞቀ ውሀ በባልዲ ቀዳን ። አብዱረህማን ሲመጣ ከኔ ዘግይቶ ስለነበር እንደመጣ ሽንት ቤት ገባ ጀናዛውን አላየውም ነበር።
" ይህ ሰው አፍሪካዊ ይመስላል የምን ሀገር ሰው ነው?" በማለት ጠየቀኝ።
ከደቂቃ በፊት ወደተመለከትኩት ጀናዛ ፊቴን አዞርኩ ሰውነቱ እንደፂሙ ጠቁሯል። ደነገጥን እንደምንም ነፍሳችንን ተቆጣጥረን ማጠብ እንዳለብን ተነጋገርን። ...... አጥበን ልክ እንደጨረስን በህይወቴ አይቻቸው የማላውቃቸው ትላትሎች ከሰውነቱ መውጣት ጀመሩ አካሉ በትላትሎች ተሸፈነ። ድንጋጤያችን ጨመረ ውስጣችን ተሸበረ በፍጥነት ከፍነን ለቀብር አዘጋጀነውና ከክፍል ወጣን።
ይዘውት ከመጡት ሰዎች መካከል አንዱን ነጠል አድርገን
" ከመሞቱ በፊት ምን አይነት ሰው ነበር?" በማለት ጠየቅነው
አላህ የከለከለውን ድንበር የሚጥስ ሰው እንደነበር ነገረን
【ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን】
ለወዳጅ ዘመድዎ ሼርና ፎርዋርድ በማድረግ ያዳርሱ
በቻናላችን በሚሰጡ ትምህርቶች ተሳታፊ ለመሆን ይህን ይጫኑና ጆይን ይበሉ
https://t.me/shekalidarashid
https://t.me/shekalidarashid
363 views$$RïYÁD MÂHRËZ$$, 16:36