2021-07-04 09:28:14
የቅዳሜ ቀደዳ 29-(፳፱)
እንደምነህ ጌታዬ? እንዴት ነሽ እናቴ? ወደ ቅዳሜያችን ተመልሰናል! እስቲ አንድ ፅድት ያለ ነገር ላጫውትህ!
.
.
.
ምን መሰለህ?
14 የአፍሪካ ሃገራት ለረጅም ዘመናት ተገደው ስለሚቀልቧት አውሮፓዊቷ ፈረንሳይ ሳስብ ይደንቀኛል!
እ.ኤ.አ ከ 1960ዎቹ በኃላ አውሮፓውያኑ አፍሪካን ተገደውም ሆነ ወደው መልቀቅ የጀመሩበት ግዜ ነበር! ታድያ በዛን ወቅት እንግሊዝን በቅኝ ግዛት ትገዳደራት የነበረችው ፈረንሳይ መካከለኛው እና ምዕራብ አፍሪካ እና አንዳንድ የሰሜን አፍሪካ ሃገራት የግሏ ነበሩ!
ፈረንሳይ የምዕራብ አፍሪካ ሃገራትን ለቃ ስትሄድ ሃገራቱን "PACT: for the continuation of colonization" የሚባል ስምምነት እንዳስፈረመቻቸው ይነገራል!
ስምምነቱ በአጭሩ እንዲህ ይላል!
"....በቀኝ ግዛት በያዝኳቹ ግዜ ፈረንሳይ ለእያንዳንዳችሁ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይን አፍስሳለች! ትምህርት ቤቶችን ሰርተናል፣ መንገድ እና ሆስፒታሎችን ገንብተናል፣ ብዙ የመሰረተ ልማት አውታሮችንም ዘርግትናል! ስለዚህ ነፃነታችሁን የምትፈልጉ ከሆነ በግዴታም ይሁን በውዴታ ይህንን ስምምነት መፈረም ይኖርባችኃል! ለእያንዳንዳችሁ ሃገራት ፈረንሳይ "CFA franc" የሚባል የመገበያያ ገንዘብ ትሰጣችኃለች! የምትገበያዩት በዚህ ገንዘብ ብቻ ይሆናል! የገንዘቡን ህትመት የምትቆጣጠረው ፈረንሳይ ብቻ ናት! እያንዳንዳችሁ የሃገራችሁን 85% የሚሆነውን ገንዘብ(reserve) የምታስቀምጡት የፈረንሳይ ማዕከላዊ ባንክ ይሆናል! እናንተ ጋር መቀመጥ የሚችለው 15% የሚሆነውን ብቻ ነው! ከዚህ የበለጠ ገንዘብ የምትፈልጉ ከሆነ የፈረንሳይን ፍቃድ መጠየቅ ይኖርባችኃል! 85% የሚሆነውን የሃገራችሁን "reserve" የፈረንሳይ የገንዘብ ሚንስትር ያስተዳድራል!...."
ይቀጥላል!
"....ምንም አይነት የጦር መሳርያ የምትፈልጉ ከሆነ መግዛት የምትችሉት ከፈረንሳይ እና ፈረንሳይ ብቻ ነው! የሃገራችሁን መከላከያ ማሰልጠን የምትችለው ፈረንሳይ ብቻ ናት! ከፈረንሳይ ፍቃድ ውጪ ከየትኛውም ሃገር ጋር የጦር(ወታደራዊ) ስምምነት መፈፀም አትችሉም! የፈረንሳይ ጦር እንደፈለገው ሃገራችሁ ውስጥ መንቀሳቀስ ይችላል!
በሃገራችሁ ውስጥ የሚካሄድ ማንኛውም ጉዳይ የፈረንሳይ መንግስትን ጥቅም አደጋ ላይ የጣለ መስሎ ከተሰማን ፈረንሳይ ወታደሮቿን ልካ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ትችላለች! የእያንዳንዳችሁ ሃገራት የስራ ቋንቋ ፈረንሳይኛ መሆን አለበት! ሃገራችሁ ውስጥ ተቆፍሮ የወጣው ብቻ ሳይሆን ለወደፊት ተቆፍሮ የሚወጣውም የተፈጥሮ ሃብት በቀደምትነት መሸጥ ያለበት ለፈረንሳይ ነው! የሃገሮቻችሁ የውጪም ሆነ የንግድ ፖሊሲ ለፈረንሳይ መንግስት በሚስማማ መልኩ መቀረፅ አለበት!..."
ጌታዬ! ይህ ስምምነት ፈረንሳይ 14 በቀኝ የገዛቻቸውን የምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ ሃገራትን ለቃ ስትሄድ ያስፈረመቻቸው ነው! ሃገራቱ ቤኒን፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ሴኔጋል፣ ኮትዲቯር፣ ማሊ፣ ኒጀር ፣ ቶጎ፣ ካሜሩን፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ጊኒ ቢሳኡ፣ ቻድ፣ ኮንጎ፣ ኢኳቶርያል ጊኒ እና ጋቦን ናቸው!
ይህ ስምምነት እውነት እንደሆነ ደግሞ የቀድሞዋ የአፍሪካ ህብረት የአሜሪካ አምባሳደር "Arikana Chihombori" ትናገራለች።
አባዬ! ፈረንሳይ "colonial Tax" ትለዋለች! በሌላ አጠራሩ "Monetary colonialism" ይባላል!
ገራሚ ሃቅ አንድ!
እነዚህ 14 ሃገራት ፈረንሳይ በሰጠቻቸው እና በምትቆጣጠረው "CFA franc" የሚባል የመገበያያ ገንዘብ እንዲጠቀሙ ተደርጓል!
ገራሚ ሃቅ ሁለት!
የእነዚህ ሃገራት 85% የሚሆነው የገንዘብ ክምችት ፈረንሳይ ማዕከላዊ ባንክ ይቀመጣል! ሃገራቱ መጠቀም የሚችሉት 15% የሚሆነውን ብቻ ሲሆን ከዛ ያለፈ ካስፈለጋቸው ፈረንሳይ መፍቀድ አለባት! እንደ አምባሳደሯ ገለፃ ፈረንሳይ ይህንን ገንዘብ ወደ "Stock market" በራሷ በማስገባት በአመት ወደ 500 ቢልዮን ዶላር ታገኝበታለች! ይህንን ገንዘብ ደግሞ መልሳ ለነዚህ ሃገራት በወለድ ታበድረዋለች! (በአጭሩ እነዚህ 14 ሃገራት በየአመቱ ለፈረንሳይ 500 ቢልዮን ዶላር ያስገባሉ!)
በነገራችን ላይ የነዚህ ሃገራት ነዳጅ፣ ጋዝ፣ ወርቅ፣ ዳይመንድ ወ.ዘ.ተ የሚጋዘው ወደ ፈረንሳይ ነው!
"Areva" የሚባለው የፈረንሳይ የኑዩክለር አምራች ኩባንያ ግብዓት የሚሆነውን "Uranium" 100% የሚወስደው ከ "Gabon" ነው!
"Total" የሚባለው የፈረንሳይ የነዳጅ ኩባንያም የሚሰራው ተመሳሳይ ነገር ነው! በአንድ ወቅት የ "Gabon" ፕሬዝዳንት የነበሩት "Omar Bongo"
"....ጋቦን ከፈረንሳይ ውጪ ሹፌር የሌለው መኪና ስትሆን፣ ፈረንሳይ ያለ ጋቦን ደግሞ ነዳጅ የሌለው መኪና ናት!..." ማለታቸው ይታወሳል!
የፈረንሳይን ተዘዋዋሪ ቀኝ ግዛት የተቃወሙ የነዚህ ሃገራት መሪዎች ታሪካቸው ግድያ ወይ መፈንቅለ መንግስት ነው!
ፈረንሳይ እ.ኤ.አ ከ 1962 እስከ 1995 ባሉት 33 አመታት 19 ጊዜ በአፍሪካ ሃገራት የፖለቲካ ጉዳይ ጣልቃ በግልፅ ገብታለች!
እ.ኤ.አ ከ 1960 ጀምሮ ደግሞ 40 ግዜ በአፍሪካ ጉዳይ ወታደሮቿን ጣልቃ አስገብታለች!
እ.ኤ.አ ከ 2010 ጀምሮ ብቻ ብትቆጥር ሊብያ፣ ማሊ፣ መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ እና ኮትዲቯር የመሳሰሉ ሃገራት ውስጥ የተካሄዱ የመንግስት ግልበጣዎች ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተሳትፋለች!
ግልፅ ምሳሌዎች!
"Mali" ነፃነት ባገኘች ማግስት የመጀመርያው የሃገረቱ ፕሬዝዳንት የነበሩት "Madibo keita" ሃገሩ ከፈረንሳይ ጫና እንድትወጣ እና የፈረንሳይን ተፅህኖ ለማስቆም ሲያስቡ መፈንቅለ መንግስት እንዲደረግባቸው እና ከዛም በእስር እያሉ እንዲሞቱ ፈረንሳይ አድርጋለች!
"Tomas Sankara" ሃገሩ "Burkina Faso" ከፈረንሳይ ጫና እንድትወጣ ጥረት ማድረግ ሲጀምር እና አዝማሚያው አላምር ሲላቸው መፈንቅለ መንግስት ተደርጎበት እ.ኤ.አ 1987 ላይ እንዲገደል ሆኗል!
እ.ኤ.አ 1963 ላይ የቀድሞው የ "Togo" ፕሬዝዳንት "Sylvanus Olympio" አዲስ የመገበያያ ገንዘብ ለሃገሪቱ ህዝብ ለማስተዋወቅ ሲሰናዳ መፈንቅለ መንግስት ተደርጎበት፣ በንጋታው በአሰቃቂ ሁኔታ ተገሎ ሬሳው "Togo" የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ አጠገብ እንዲጣል ተደርጓል!
የ "Benin" ፕሬዝዳንት የነበሩት "Hubert maga" እና የ"Libya"ው "Gadafi" መወገድ ጀርባም ፈረንሳይ አለች!
አሁን እንኳን የኮትዲቯር መንግስትን ደግፋ ስልጣን ላይ ያስቀመጠችው ፈረንሳይ ናት! አባዬ! እንደምታውቀው ደግሞ ፈረንሳይ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ "ቡና" እና ለቸኮሌት ግብዓት የሚሆናትን "Cocoa" የምትገዛው ከኮትዲቯር ነው።
ጌታዬ! የቀድሞው የፈረንሳይ ፕሬዝድንት "Jacques Chirac" ያሉትን ታስታውሳለህ?
"....We have to be honest and acknowledge that a big part of the money in our banks comes precisely from the exploitation of the African continent!... "
1.2K views Bĩnyam , 06:28