2022-04-22 06:51:30
በትንሣኤው ምን አገኘን!!!
ጌታ ኢየሱስ የተነሳው ሞትን ድጋሚ ላይሞትና ደግሞም ሞት የማይዘውን ሕይወት ይዞ ነው!
የጌታ የኢየሱስ ትንሳኤ ሁሉን ነገር ማለትም አካሄድን፣ የሕይወትን ዘይቤ እና የሰዎችን አስተምህሮ አስቀይሯል።
ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሳቱ እኛ ምን አገኘን?
1. ዳግመኛ ውልደት
ዮሐንስ 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁵ ኢየሱስም፦ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤
²⁶ ሕያው የሆነም የሚያምንብኝም ሁሉ ለዘላለም አይሞትም፤ ይህን ታምኚያለሽን? አላት።
ዳግመኛ መወለድ የትንሳኤው ውጤት እና ከትንሳኤውም ጋር የተገናኘ ነው። ትንሳኤ ለአሮጌው ሕይወት ሞተን በክርስቶስ ለአዲሱ ሕይወት ጅማሮ ነው።
አዲሱ ሰው እንዲነሳ አሮጌው ሰው መሞቱ መሠረት ነው።
2. ሕያው ተስፋ
በ 1ኛ ጴጥሮስ 1:3 ላይ "ሕያው ተስፋ" ያለው ምኑን ነው? በሰማይ ለማይጠፋ፣ ለማይበላሽ፣ ለማይለወጥ ርስት የተወለድንበትን ነው።
የእኛ የመዳን ተስፋ የማይጠፋ፣ የማይበላሽ፣ የማይለወጥ ርስት ሆኖ በእግዚአብሔር መንፈስ ተጠብቆ ወደፊት ለእኛ ይገለጣል። የምንጨርሰው እዚህ ምድር ላይ አይደለም እዚህ ምድር የምንቆየው ያለንን ለተልዕኮ እስክንጨርስ ብቻ ነው።
3. ጽድቅ
“ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው።”
— ሮሜ 4፥24-25
4. አለመጥፋት
1ኛ ቆሮንቶስ 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵³ ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና።
⁵⁴ ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ፦ ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል።
5. ተስፋን
1ኛ ተሰሎንቄ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ አንቀላፍተው ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን።
¹⁴ ኢየሱስ እንደ ሞተና እንደ ተነሣ ካመንን፥ እንዲሁም በኢየሱስ ያንቀላፉቱን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ያመጣቸዋልና።
We Christian have living hope because of the resurrection of Jesus Christ from the dead.
የኢየሱስ ትንሳኤ የክርስትናችን መሰረት ነው!
በመጨረሻም እኛ በትንሳኤው የምናምን የትንሳኤው ልጆች ስንሆን ከሰዎች ሁሉ ይልቅ የተባረክን እና ደስተኞች ነን! እንዲሁም የትንሳኤውን ምስጢር መረዳታችን ከሌሎች ሰዎች ይለየናል። ይህን የሚያደርግው ሕያው ተስፋው ነው።
መልካም ቀን
101 views♪♫•*¨*•.¸¸ ▂▃▄▅▆▇█▓▒░ብላቴናው ተፈሪ░▒▓█▇▆▅▄▃▂ ¸¸.•*¨*•♫♪, 03:51