የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በዕረፍት ጊዜያቸው ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ የድርሻቸውን እንዲወጡ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ጥሪ አቀረቡ፡፡ ሚኒስቴር ዴኤታው ጥሪያቸውን ያቀረቡት ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ዳውሮ ታርጫ ካምፓስ ተማሪዎችና የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ ጋር ሐምሌ 14 ቀን 2011 ዓ.ም በከተማው ችግኝ በተከሉበት ጊዜ ነው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር @MINISTERY_OF_EDUCATION 335.3K views16:14