Get Mystery Box with random crypto!

💜 ...ማርያምን ...🕯

የቴሌግራም ቻናል አርማ mezmure_tewahdo — 💜 ...ማርያምን ...🕯
የቴሌግራም ቻናል አርማ mezmure_tewahdo — 💜 ...ማርያምን ...🕯
የሰርጥ አድራሻ: @mezmure_tewahdo
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.85K
የሰርጥ መግለጫ

/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮን
የጠበቁ መዝሙሮች ና የቅዱሳን ገድል
ይገኙበታል
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"
''የቅዱሳንን ክብራቸውን እናገር ዘንድ ፍቅር ያስገድደኛል''
✍️ግሩፑ ላይ መዝሙር ብቻ አይደለም
የተለያዩ ነገሮችንም ታገኙበታላችሁ
🙏 ኑ በጋራ ሁነን እንማር
👇
❷❶ ማርያም ሆይ እኖድሻለን
ለማንኛውም አስተያየትና ሀሳብ
@joni_21_27
👆👆

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-05 11:30:15 •➢ ሼር // SHARE

@Mezmure_tewahdo
@Mezmure_tewahdo
709 views08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 11:30:00 ምስጋናው ይቀጥል


ምስጋናው ይቀጥል ዝማሬው ይቀጥል
እግዚአብሔር ስላለ ከያዘ የማይጥል
በምናየው ነገር በምንሰማው ወሬ
እንዳይቆም ምስጋና እንዳይቆም ዝማሬ


የሰማእታቱ ደም የፈሰሰው በምድር
አይተናል ሲያስቀጥል የክርስትናን ዘር
እንድናምን ብቻ መች ተጠራን እና
በእሳቱም መካከል ቅኔ አለን ምስጋና

አዝ___

መች ማጥፋት ይቻላል እሳትን በእሳት
አይቆምም ማህሌት ቅዳሴ ሰዓታት
ከሰማዩም በላይ ከሰማዩም በታች
ቤተ ክርስቲያን ዛሬም ነገም አለች

አዝ___

የዓለም ጨው ሆነን በዓለም የበዛነው
እየተደበደብን እየተገፋን ነው
በገደሉን ጊዜ ቁጥራችን ይበዛል
ከሞትም በኃላ ሂወት ይቀጥላል

አዝ___

የተስፋይቱን ምድር ተነሱ እንወርሳለን
በመዝሙር በእልልታ ቅጥሩን እያፈረስን
የሰላዮቹን ቃል ሰምታችሁ አትፍሩ
በሃይማኖት ጽኑ በእምነታችሁ ኑሩ

•➢ ሼር // SHARE

@Mezmure_tewahdo
@Mezmure_tewahdo
734 views08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 22:06:40
አባታችን ከዚህ

ከንቱ አለም አረፉ
1.2K views19:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 10:28:47 አዳምጡት እስቲ አትለፉት

#ሼር_አርጉት
@Mezmure_tewahdo
@Mezmure_tewahdo
1.8K views07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 17:34:43
ለምን ጠላኽኝ

ለምን ጠላኽኝ ወንድሜ ያንድ አባት ልጆች እኮነን
ለምን ጠላኽኝ ወንድሜ ያንድ እናት ልጆች እኮነን
ብዙ ነው መንግስቱ አብረን እንወርሳለን
ሰፊ ነው ግዛቱ አብረን እንወረሳለን
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የተካፈልኩትን ንብረት አጥፍቼ ብመለስ ዛሬ
አባቴ ናፍቆኝ ብመጣ ልቤን አንገቴን ሰብሬ
ለሁላችንም ይበቃል ብዙ ነው የሱ መንግስት
አይክፋህ ባክህ ወንድሜ ፍቅር ይበልጣል ከሀብት
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ፊትህ በሃዘን አይጥቆር ድንጋዩን ጣለው ወንድሜ
ተቅበዝባዥ እንዳያደርግህ እጅህ ቆሽሾ በደሜ
ልብህን መልካም ብታደርግ ያንተም መስዋት ያርጋል
ጌታ ለሁሉም እኩል ነው መታዘዝ ንጉስ ያደርጋል
፡፡፡፡፡፡፡፡
ብልጥ ሰለህንሁ አይደለም የተባረኩት በጌታ
ጽኑ መሻቴን አይቶ ነው በኩር ያደረገኝ ስመታ
የበቀል ጦርህን ሸሽቼ በባእድ ሀገር ብኖርም
በልጅ በትዳር ባርኮኛል አብረን እንኑር በሰላም
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ለምን ጠላኽኝ ወንድሜ ያንድ አባት ልጆች እኮነን
ለምን ጠላኽኝ ወንድሜ ያንድ እናት ልጆች እኮነን
ብዙ ነው መንግስቱ አብረን እንወርሳለን
ሰፊ ነው ግዛቱ አብረን እንወርሳለን

#ሼር_አርጉት
@Mezmure_tewahdo
1.4K views14:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 18:34:43
እናቴ ማርያም

"#የኃጢአቴ ቁስል ያላንቺ ጸሎት እንዳይድን ልዑል እግዚአብሔር ያውቃልና፣ #ኃጢአቴ ከዓለም ሁሉ ኃጢአት እንዲበልጥ ተረዳ፣ ንጽሕናሽ ደግሞ ከቅዱሳን ሁሉ ንጽሕና #እንዲበልጥ እንዲበዛ ዐወቀ። ስለዚህም #ፍቅርሽን በልቡናዬ ጨመረ። ጽኑ ቁስል ያለ ጽኑ ዕፁብ ድንቅ መድኃኒት እንዳይጠግ ያውቃልና።

...የእግዚአብሔር የጥበቡ ርቀት ምን ይረቅ ምን ይጠልቅ? ...ደግነቱና ይቅርታውንስ ማን ይናገራል #በኃጢአት ቁስለኞች ፊት መድኃኒት አዘጋጀ። ተቀብተው በእርሱ እንዲድኑ ነው።

ድንግል ሆይ፤ የእኔን አመንዝራነቴን እናገራለሁ ያንቺን ንጽሕና የልጅሽኝ ቸርነት #አወራለሁ። ድንግል ሆይ የኔን ስሕተት ያንቺን ማማለድ የልጅሽንም መታገስ #እናገራለሁ። ድንግል ሆይ የኔን ስንፍና ያንቺን ምክር የልጅሽንም ይቅርታ እናገራለሁ።"

የፍቅሯ ኃይል ካረፈበት፣ የስሟም አጠራር ከአንደበቱ ከማይጠፋ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገኘ የልመና ቃል
(አርጋኖነ ማርያም ዘአርብ
)


•➢ ሼር // SHARE

@Mezmure_tewahdo
@Mezmure_tewahdo
1.4K views15:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 21:11:31
እናት አለኝ የምታብስ እንባ ....16

@Mezmure_tewahdo
1.8K views18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 12:04:16 የካቲት 12 ፦ አንድ ችግረኛ ሰው ያለ ሥራ ቁጭ ብሎ ቅዱስ ሚካኤል ምግብ
እንዲያመጣለት በመነዝነዝ ያስቸግረው ስለነበረ ቅዱስ ሚካኤልም ወደ
ችግረኛው ሰው በመሄድ ‹‹ወይ እርሻ ኖሮህ አልባረኩልህ፣ወይ ገንዘብ ኖሮክ
ንግድህን አልባረኩልህ ዝም ብለህ ለምን ታስቸግረኛለህ›› ብሎት ወቅሶት
በቅዱስ ሚካኤል ገንዘብ ነግዶ ተአምር የሰራለት ቀን ነው፡፡
መጋቢት 12 ፦ ኢአማኒ የነበረውን ቂሶንን ወደ ክርስትና የመለሰበት ቀን ነው፡፡
ሚያዝያ 12 ፦ ነብዩ ኤርሚያስን በአመጸኛው ሴዴቅያስ ከተጣለበት የቆሻሻ
ጉድጓድ ያወጣበት ቀን ነው፡፡
ግንቦት 12 ፦ ወደ ነብዩ ዕንባቆም ተልኮ ዕንባቆምን በባቢሎን ዳንኤልን
በአንበሳ ጉድጓድ በተጣለበት ጊዜ ምግብ እንዲያደርስለት ከምድረ
ፍልስጥኤም በተአምር ተሸክሞ ፋርስ አውርዶት ዳንኤልን የረዳበት ቀን ነው፡፡
ሰኔ 12 ፦ ቅድስት አፎሚያን ከሰይጣን የታደገበት ቀን ነው፡፡ ባሕራንንም የሞቱን
ደብዳቤ አጥፍቶ፣በሠርግ ተክቶ ተአምር እንደሰራለት ድርሳኑ ይነግረናል፡፡
ሐምሌ 12 ፦ እግዚአብሔር የይሁዳ ንጉሥ የሕዝቅያስን ጸሎት ሰምቶ ቅዱስ
ሚካኤልን ልኮለት ከሰናክሬም መቅሰፍት ኢየሩሳሌምንና የይሁዳ ሰዎችን
ያዳነበት ቀን ነው፡፡
ነሐሴ 12 ፦ ንጉሡ ቆስጠንጢኖስን የረዳበት፤አርባ ዘመን ቤተ ክርስትያንን
ሲያቃጥሉ ክርስትያኖችን በእሳት ሲማግዱ፣በሰይፍ ሲያርዱ የነበሩትን
ዲዮቅልጥያኖስንና መክስምያኖስን ከምድረ ገጽ ያጠፋበት ቀን ነው፡፡
ሺህ በክንፉ ሺህ በአክናፉ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በብርሃናዊ ክንፉ አቅፎ
ደግፎ ከክፍ ነገር ይሰውረን፡፡ የቅድስት አፎሚያ፣የቅዱስ ላሊበላ ጸሎት በረከት
ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡


ሼር በማድረግ ለወዳጆ
በቅዱስ ሚካኤል ስም ይዘክሯቸው፡

@Mezmure_tewahdo
@Mezmure_tewahdo
2.3K views09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 12:04:16 ሰኔ 12 የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል! እንኳን አደረሳችሁ!
የቅድስት አፎሚያ እና የቅዱስ ላሊበላ እረፍት ነው!
በቀሲስ መ/ር ሄኖክ ወ/ማርያም
ሰኔ 12 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ደገኛዋን ቅድስት አፎሚያን ከሰይጣን ተንኮል
የታደገበት ዕለት እንደሆነ ድርሳኑ መዝግቦልናል፡፡
ቅድስት አፎሚያ አስተራኒቆስ የተባለ ደግ ባል ነበራት፡፡ ይህ ሰው ሊሞት ሲል
የቅዱስ ሚካኤልን ስዕል አዘጋጅቶ በመስጠት፤በየወሩ በቅዱስ ሚካኤል ቀን
ለድሆች፣ለጦም አዳሪዎች ምጽዋት እንድትሰጥ፤መስጠት ብቻ ሳይሆን ወደ
ፈጣሪዋ አጥብቃ ከመጸለይ እንዳታቋርጥ ነግሯት ያርፋል፡፡
ቅድስት አፎሚያም ይሄንን ርህራሄና ሰብአዊነት የተመላበት በጎ ሥራ አጥብቃ
መስራት ጀመረች፡፡ የበጎ ነገር ጠላት የሆነው ሰይጣን የቸርነት ሥራዋን
ተመልክቶ ወደ ቅድስት አፎሚያ መጣ፡፡ አዛኝ በመምሰልም ‹‹ለምን ገንዘብሽን
ታባክኛለሽ፤ይልቁንስ ገንዘብሽ ከማለቁ በፊት ባል አግብተሽ አትኖሪም ባልሽ
እንደሆነ ጸድቋል ምጽዋት አያስፈልገውም›› አላት፡፡
ሰይጣን የአስተራኖቆስን መጽደቅ የተናገረው አፎሚያን ለማስደሰት ሳይሆን እንደ
አዳምና ሔዋን ለማሳት ነው፡፡ ዘፍ 3÷1-8
ቅድስት አፎሚያም ‹‹ሌላ ባል ላላገባ ከፈጣሪዬ ጋር ቃል ኪዳን ገብቻለሁ››
አለችው፡፡ ሰይጣንም የሚያስትበት የጥፋትና የተንኮል መንገድ ብዙ ነውና
መነኩሴ በመምሰል ብዙ ቢዘበዝባትም አፎምያ ግን ለሥጋዊ ምክሩ ቦታ
ሳትሰጠው እንቢኝ አለችው፡፡
ሰይጣንም በዚህ ሳያበቃ ያስትልኛል፣አፎሚያን ያሳምንልኛል ያለውን ሐሳብ
እያመጣ ቢነግራትም በእንቢታዋ ጸናች፡፡ ለሰይጣን ውሸት የየዕለት ሥራው
ስለሆነ ይባስ ብሎ ቅዱስ ሚካኤል ነኝ ብሎ እርፍ አለው፡፡ ሰይጣን በአምሳለ
መልአክ ሰውን እንደሚያስት ያወቀው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ሰይጣን ራሱን የብርሃንን
መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣል›› ብሎ ነግሮናል፡፡ 2ኛ ቆሮ 11÷14
ስለዚህ አፎምያ በቅዱስ ሚካኤል ተመስሎ ቢነግራትም አልቀበልም አለችው፡፡
ወዳጆቼ እስቲ እራሳችንን እናስብ ስለ እውነት እኛ ብንሆን ይህንን ፈተና እናልፍ
ነበር? ይህ የአፎሚያን የእምነት ጥበብ የሚያሳይ ነው፡፡
ሰይጣንም አሉኝ የሚለውን ሰይጣናዊ ማሳመኛ ጥበብ ተጠቀመ፡፡ አፎሚያም
ምንም ይበል ምንም አለተቀበለችውም፡፡ ምክንያቷ ደግሞ ንግግሩና ገጽታው
ስላልተካከለ፡፡
በአፎምያ መንፈሳዊ ቆራጥነት የተበሳጨው ሰይጣንም ዓይኑን አፍጥጦ፣ጥርሱን
አግጥጦ አንቆ ሊገላት ሲል ቅዱስ ሚካኤል ብርሃናዊ ክንፉን እያማታ በቅጽበት
ደረሰላት ከሰይጣንም እጅ አዳናት፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ስለ እረፍቷ ‹‹ብጽዕት
አፎሚያ ሆይ ሄደሽ የቤትሽን ሥራ አዘጋጂ፣ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት
ትለያለሽ፣እነሆ እግዚአብሔር ዓይን ያላየውን፣ጆሮም ያልሰማውን፣በሰው ልብ
ያልታሰበውን አዘጋጅቶልሻል›› ብሎ የምስራቹን ነግራት ከእሷ ተሰወረ፡፡
ቅድስት አፎምያም የቅዱስ ሚካኤልን የበዓሉን ዝግጅት ከፈጸመች በኃላ ወደ
ኤጲስቆጶሱና ወደ ካህናቱ መልዕክት ላከች እነሱም መጡ፡፡ ለእነሱም ቀሪ
ገንዘብዋን ለድሆች ለጦም አዳሪዎች ይሰጥዋቸውም ዘንድ አስረከበቻቸው፡፡
ከዚህ በኃላ ተነስታ ጸለየች፣የከበረ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልንም ሥዕል አንስታ
አቅፋ ሳመችው/አፎሚያ ለሰይጣን ይህንን ስዕል ስታሳየው ነው አሳች መልኩ
ወደ ሰይጣንነት የተቀጠረው/ ያን ጊዜም ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለየች፡፡ ቅዱስ
ሚካኤልም የከበረች ነፍሷን በብርሃናዊ ክንፉ አቅፎ ደግፎ የፈጣሪውን
መንግስት እንድትወርስ አድርጓታል፡፡
ከቅድስት አፎምያ ሁለት ነገር እንማራለን፡፡ አንደኛው ጥቅም አዘል ፈተናን አልፋ
ሰይጣንን ድል መንሳትዋ ሲሆን ሁለተኛው አፎምያ ጽድቅ ሰርታ የሥጋ ፈተናዋን
ድል ነስታ፣ሰይጣንን ማሸነፍ የቻለችው ጫካ ገብታ ሳይሆን በዓለም ሆና ነው፡፡
ስለዚህ ጽድቅ ሰርቶ ለመጽደቅ ሥራ እንጂ ቦታ እንደማይወስነው ታሪክዋ
አስተማሪ ነው፡፡
፨ ሰኔ 12 ቀን እረፍቱ ለቅዱስ ላሊበላ ፨
ቅዱስ ላሊበላ በነገሠ ጊዜ እኔ ንጉሥ ነኝ ብሎ ድሆችን ሳይንቅ፣በአገዛዙ ሰዎችን
ሳያስጨንቅ የኖረ ጻድቅ ነው፡፡ ጌታችን ቅዱስ ላሊበላን የፍቅሩን ጽናት በማየት
መልአኩን ላከለት፡፡ መልአኩም ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማይ ነጠቀው፡፡ በዚያም
ቤተ ክርስትያንን እንዴት እንደሚያንጽ ጥበብን ገለጠለት፡፡
ቅዱስ ላሊበላም ሥጋ የለበሱ ሰዎች ሳይሆኑ ቅዱሳን መላእክቶች በስውር
እየተራዱት እነዛን አስደናቂ፣ለውጭ ጥበበኞች አጨቃጫቂ የሆኑትን ፍልፍል
አብያተ ክርስትያናትን አንጿል፡፡
ጌታችንም ሰኔ 12 ቀን በብርሃን ሰረገላ ተቀምጦ፣የሚያስፈራ መብረቅን ተጎናጽፎ
ቅዱሳን መላእክትን አስከትሎ ወደ ቅዱስ ላሊበላ መጣ፡፡ ጌታም ‹‹ወዳጄ
ላሊበላ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁንልህ፡፡ እኔ በማይታበል ቃሌ
እነግርሃለሁ፤ማደርያህ በክብር ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር ይሁን፡፡ በጸሎትህና
በቃል ኪዳንህ ለሚታመን እምነቱ እንደ ጴጥሮስና ጳውሎስ ደም መፍሰስ
ይሆንለታል፡፡
ወደ ቤተ መቅደስህ የሔደ ኢየሩሳሌም ወዳለው ቤተ መቅደስ እንደ ሄደ
ይሆንለታል፡፡ መቃብርህንም የተሳለመ የሥጋዬን መቃብር እንደተሳለመ
ይሆንለታል፡፡ በየወሩ የተራቡትን እያበላ፣የተጠሙትን እያጠጣ መታሰብያህን
ለሚያደርግ እኔ የተሰወረ መና እመግበዋለሁ፤የህይወትንም ጽዋንም
አጠጣዋለሁ፡፡ በመታሰብያህ ቀን ዕጣን ወይም ስንዴ የሚያገባውን እኔ
በኢየሩሳሌም ሰማያዊት በውስጠኛው መጋረጃ አስቀምጬ ከተቆረሰው ሥጋዬ
አቆርበዋሁ፤በአማላጅነትህም እየታመነ የገድልህን መጽሐፍ የሚጽፈውን ያንተ
ስም በተጻፈበት ቦታ እኔ ስሙን እጽፋለሁ፡፡፡ በፍጹም ልቡ ለሚያምን ይህን
የማይታበል ቃል የተናገርኩ የህያው እግዚአብሔር ልጅ እኔ ኢየሱስ ነኝ›› አለው፡፡
ቅዱስ ላሊበላም ይህንን ቃል ኪዳን ስለሰጠውና ስላጸናለት ጌታችንን እያመሰገነ
እግሩ ላይ ወድቆ አመሰገነው፡፡ ሰኔ 12 ቀንም አረፈ፡፡ ቅድስት ነፍሱንም ቅዱሳን
መላእክት ይዘው የዘላለም ማረፍያው አስገቡት፡፡
፨ የቅዱስ ሚካኤል የወር በዓላት ከነምክንያት ፨
መስከረም 12 ፦ ቅዱስ ፋሲለደስን በመከራው ሰዓት የረዳበት እና የሰማዕትነት
ተጋድሎውን ከፍጻሜ እንዲያደርስ ከጎኑ ተገኝቶ ያጸናበት
ጥቅምት 12 ፦ ነብዩ ሳሙኤል ዳዊትን ቅብዐ መንግስት እንዲቀባው የነገረበት
ቀን ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊትም ከቅዱሳን መላእክት ረድኤት በደንብ ስለተጠቀመ
ክብራቸውን በመዝሙሩ በደንብ መዝግቧል፡፡
ህዳር 12 ፦ የቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሲመቱ ነው፡፡ በዚህ ቀን እግዚአብሔር
የመላእክት አለቃ አደርጎ ሾመው፡፡ የመላእክት ሹመት እንደ ሰው በተጽእኖ
አይደለም፡፡ ሰው በሰው ላይ የሚሾመው ለመገልገል ነው፡፡ የመላእክት ሹመት
ግን ለማገልገል ነው፡፡ እንደ ሰው አንዱ መልአክ አንዱን መልአክ አያገለግልም፡፡
አገልግሎታቸው እግዚአብሔርንና ሰውን ነው፡፡
በዚህም ቀን ለሰው ልጆች ከፈጣሪው ምህረት የሚለምንበት እና በቃል ኪዳኑ
ነፍሳትን ከሲኦል የሚያወጣበት ቀን ነው፡፡ ለነዌ ልጅ ለኢያሱ በታላቅ ክብር
በንጉሥ ጭፍራ አምሳል የታየበት ቀንም ነው፡፡
ታህሳስ 12 ፦ ዱራታኦስና ቴዎብስትያን የረዳበት ቀን ነው፡፡
ጥር 12 ፦ ያዕቆብን ከኤሳው፣ተላፊኖስን ከአመጸኛው ያዳነበት ቀን ነው፡፡
1.8K views09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 11:40:39
#ባህራን_ነኝ !
ፈጣሪዬን የዘነጋው
መኖር የሚያጓጓኝ
አዳኜን የማላውቅ
ለሞት የተጠራው
መድረሻዬን የማላውቅ

#ሚካኤልም_መጣ
ታሪኬን ሊለውጥ
ህይወትን ሊሰጠኝ
ለክብርም ሊያበቃኝ
ባህራን እኔ ነኝ ያውም የሚካኤል ወዳጅ
1.3K views08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ