*ድንግል ትንሳኤሽን* ድንግል ትንሳኤሽን እስከምናይ ድረስ ገብተናል ሱባኤ በአንድነት በመንፈስ ለእኛ እስከሚገለጥ ቶማስ ያየው እውነት አንወጣም ከደጅሽ ኪዳነ ምህረት (፪) ሞትን የረገጠ ልጅሽ ካንቺ ጋር ነው ውጦ የሚያስቀርሽ የቱ መቃብር ነው የዕርገትሽን ዜና ከቶማስ ሰምተናል ትንሳኤሽ እውነት ነው ሰበንሽን አይተናል ሞትማ በሞት ተሽንፏል ባንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛል (፪) አዝ = = = = = = ልናየው ወደድን የቶማስን ክብር ለምን ተስወረን የትንሳኤሽ ምስጢር በራችንን ዘግተን በፀሎት ወድቀናል ተገልጠሽ አብሪልን ልጆችሽ ናፍቀናል ሞትማ በሞት ተሽንፏል ባንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛል (፪) አዝ = = = = = = መዝሙረኛ አባትሽ ዳዊት ጽፎልናል ሞትን የማያይ ስው ማን አለ ብሎናል ይህ እውነት በዘመን አንቺ ላይ ቢደርስም በሞት ተሽንፏል መቃብር አይኖርም ሞትማ በሞት ተሽንፏል ባንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛል (፪) አዝ = = = = = = ቶማስ ከደመናው ወርዶ ሲያናግረን ስለ ሆነው ነገር እጅጉን ተመሰጥን እኛም ይህን ክብር ተመኘን ለማየት ድንግል አሳስቢልን ኪዳነ ምህረት ሞትማ በሞት ተሽንፏል ባንቺ ላይ እንዴት ኃይል ያገኛል(፪) መዝሙር በሊቀ መዘምራን ዲ/ን ቴድሮስ ዮሴፍ > ኢሳ ፶፰ ፥ ፩-፲፬ 1.9K views18:17