2022-03-15 23:34:15
#inbox_yetalake_Melikt
ትውልድ
-----------------------
ትምህርት ሚንስቴር የ 2013/14 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ላይ #በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ግፍ ነው የሰራው።
1- ገና ሲጀመር የ10ኛ ክፍል ማትሪክ ፈተና ያለ ምንም #ስርቆት ከተጠናቀቀ ቦሀላ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ማለፊያውን በጣም ዝቅ በማድረግ ወዳቂውን ተማሪ እንደገፍ ማሳለፍ።
2- በ11ኛ ክፍል የት/ት ዘመን 2012 በተከሰተው የኮሮና ወረርሽኝ 2ኛው ሴሚስተር #ሳይማሩ ቀርቷል፣ እንዲሁ ተማሪዋቹ ከ8 ወር በላይ ያለ ት/ት ቤታቸው እንዲቀመጡ ተደርጓል። እናም ተማሪዎች በ2013 አ/ም የ11ኛ ክፍልን #ሳይጨርሱ 12ኛ ክፍል እንዲገቡ ተደረገ።
4- ከዛም የመንግስት ት/ት ቤት ተማሪዎች 12ኛ ክፍልን ሲማሩ ግን እንደድሮው በተከታታይ ቀናት አልነበረም፤ በሳምንት #ሶስት ቀናት ነበር የተማሩት፣ በተመሳሳይ የግል ት/ት ቤቶች ግን #ሙሉ ሳምንቱን አንድም ቀን ሳይዘሉ ነበር ሲያስተምሩ የከረሙት።
5- ይህ ታድያ ለአብዛኞቹ የመንግስት ት/ት ቤቶች መፅሀፍትን ለመጨረስ #በቂ ጊዜ አልነበረም። በግል ት/ት ቤቶች ግን መፅሀፍትን በተያዘላችው ጊዜ መጨረስ ችለዋል።
6- እንዲሁም በ2013 በተቀሰቀሰው ጦርነት፥ በጦርነት አካባቢዎች የነበሩ #ተማሪዎች ለጥናት እና ለመማር ማስተማር አስችጋሪ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ነበር ያሳለፉት።
እንደ ከዚ በፊቱ መንግስት የ12ኛ ክፍል ማትሪክ ፈተና በሚሰጥባቸው ቀናት #የኢንትርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ይዘጋል ተብሎ ሲጠበቅ ነበር። ነገር ግን አገልግሎቱ በ #VPN እንዲሰራ ተደርጎ ነበር።
ፈተናዎቹ ሲሰጡ በነበረው መጭበርበር ሙሉ በሚባል ደረጃ ፈተናዎቹ በተለያዩ ማህበራዊ ድህረገፃች #ተለቀቁ።
ላንብብ ብሎ ደብተሩን የያዘው ተማሪ እንደ ጅል ጥናቱን ትቶ ስልኩን ይዞ የነበረው እንደ ብልህ ነው የታየው። ፈተናዎች በ #Telegram #tiktok... በስርአት በቀይ እስብርቶ መልሳቸው ተከቦበት ነበር የወጡት። ከዚህም ባለፈ ፈተናዎቹ ከባድ ነበሩ የመንግስት ተማሪዎች በፍፁም #ያልተማሯቸው የ 11ኛ ክፍል 2ኛ ሴሚስተር እና እና የ12ኛ ክፍል ጥያቄዎች ተካተውበት ነበር።
ታድያ ይህን ሁሉ በመረዳት መንግስት ተማሪዎችን መርዳትና መደገፍ ሲገባው ጭራሽ ማለፊያው ታይቶ #በታሪክ የማይታዋቅ ሆኗል።
ከዚህም ይባስ ተብሎ በመጨረሻ ቀን የተሰጠው #የCIVIC ፈተና በቀን ብዛት ወሬው ደርሶት ከተለቀቀው የሰራው ምስኪኑ ተማሪ ስለበዛ #የCIVIC ፈተና እንዳይያዝ ተደረገ።
ማለትም ለተፈጥሮ ሳይንስ ከ #600 እንዲያዝ ፤ ለማህበራዊ ሳይንስ ከ #500 እንዲያዝ ሆነ።
አስተውሉ
ማለፊያ ለወንድ በ ተፈጥሮ ሳይንስ #363
ይህ ማለት ፈተናው ከ 700 የሚያዝ ቢሆን ማለፊያ #423 ሊሆን ነው ማለት ነው።
ከዚ በፊት የሚታወቀው የግል ሴክተሩ በደንብ እንዲሰራበት ማለፊያ ዝቅ ሲደረግ ነበር ባሁኑ ግን እንዲያውም #300 ሆኗል።
#የደሀ ልጅ ጎዳና ላይ ይውደቅ የሚል ውሳኔ ተላልፏል። ከአንድ ት/ት ቤት እንዴት ሁሉም ተማሪ ይወድቃል? በአሁኑ የታየው እንግዲ ይሄው ነው ከአንድ ት/ት ቤት አንድም ሰው ማለፍ ያልቻሉባቸው ብዙ የ መንግስት ት/ት ቤቶች ናቸው።
ተማሪ እንዳይማር የሚደረግበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።
ት/ት ሚኒስቴር በአስቸኳይ ማስተካከያ ያድርግ #ማለፊያ በደንብ ይቀንስ፣ #ለግል መግቢያም ያስተካክል እናም በጦርነቱ ለተጎዱ አካባቢዎች በደንብ ማስተካከያ ይወሰድ።
@Mettihighschoolbot
279 viewsedited 20:34