#MekdelaAmbaUniversity
ስቴም ፓውር በመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ትምህርቶች ቤተ ሙከራ/ስቴም ማዕከል አደራጅቷል።
ማዕከሉ የምህንድስና ትምህርት መርጃ መሳሪያዎች/Electronics Lab እና የ3-D ዲጂታል ማተሚያ መሳሪያዎች የተሟላለት ነው፡፡
የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና ሂሳብ ትምህርቶች (STEM) ማዕከሉ፤ ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች አገልግሎት እንዲሰጥ የተደራጀ መሆኑ ተገልጿል።
የማዕከሉ መምህራን ከቤተ ሙከራው መሳሪያዎቹ አሰራር ጋር የሚያስተዋውቅ ስልጠናም ተሰጧቸዋል።
ማዕከሉ በአካባቢው የሚገኙ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ የሚማሩትን በተግባር እንዲሞክሩና ወደ ፈጠራ ሥራ እንዲቀይሩ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡
Share&forward
Join
@merejamnch
@merejamnch