2022-04-29 18:57:45
የአይኔ እንግዳ
ክፍል 6
በእውነተኛ የፍቅር ታሪክ ላይ የተመሰረተ
እሱ የኔን ትኩረት ለማግኘት በሚያደርገው ጥረት ይበልጥ እየጠላሁት እየጠላሁትመጣው።
እኔን ለማናገር ና ትኩረቴን ለመሳብ መሞከር የቀን ከቀን ተግባሩ ሆኗል።
ሲጠጋኝ ስሸሸው ሲጠጋኝ ቀናት አለፉ ሳምንታት ተቆጠሩ ወራቶች ነጎድ ።
ጥሩም መጥፎም ጎኑ ወይም ጠንካራውም ደካማውም ጎኑ አንድ የሆነበት ሰው አይታችሁ ታውቃላችሁ? ያሰው ማለት እኔ ነኝ።
እንዴት እንዲአልሽ ልትሉኝ ትችላላችሁ ምክንያቱም
ሳልወድ በግዴ ነባን ያናገርኩበት ስለሆነ።
ወንድም ይሁን ሴትም ብቻቸውን ከተቀመጡ ምንሆንክብኝ ምን ሆንሽብኝ ወይም ምነው ብቻክን ምነው ብቻክን ብዬ ማዋራት መለያዬ ነበር የዛሬን አያድርገውና።ምክንያቱም ለመጨረሻ ጊዜ ያናገርኩት ነባን ነበር።
እኔዴት እንደ ነበር አሁንም ድረስ ትዝይለኛል። ቀኑን ባላስታውሰውም በትምህርትቀን እንደ ነበር ግን አስታውሳለሁ ።
እረፍት ተደውሎ በጀማሆነን በነ ነባ ክላስ በኩል ስናልፍ ድንገት ወደ ግራ ስዞር ነባን አየሁት እንደሌላ ጊዜው ግን አልነበረም ጥግይዞ ብቻውን ተክዟል።
የሆነ የማላውቀው ስሜት ተሰማኝ ሰውነቼን በሙሉ የሆነ ነገር ሲወረኝ ተሰማኝ።
እናም ለጓደኞቼ ምንሆኖብኝ ነው ብዬስጠየቃቸው እንዳትሞክሪው ነበረ መልሳቸው። እንዴ ለምን ስላቸው ትሰሚናለሽ ኑሀ ነቢል ማለት አንቺ እንደምታውቃያቸው ሰዎች አይደለም።
እንደለመድሽው ምን ሆንክብኝ በይውና ከምታስቢዉ በላይ ነው የሚጎዳሽ አሉኝ።እኔግን አሁንም ሀሳቤ እሱጋ መሄድ ነበር።
እሺ እንደዚደብሮት ዝም ብዬው ልለፍ ስላቸው በ1ድምፅ ነገርንሽ አይደል እኔዴ አሉኝ።አሁንም አልተዋጠልኝም ።
እኔኮ ኑሀሚን ነኝ ራሴን አውቀዋለሁ በራሴም እተማመናለሁ ስለዚ ምንም አይፈጠርም አልኳቸው ።የሆነ ነገር ሊያደርግሽ ይችላል አሉኝ።
እንደዚ አይነት ቃላት በተጠቀሙቁጥር ቀስበቀስ እልህ ሲይዘኝ ይሰማኝ ጀመር።አሁኑኑ ይህን ሀሳብ ከጭንቅላትሽ አውጪ አሉኝ።እናም ተስማማው።
ከዛ ግን ልክ አጠገቡ ስደርስ ጥዬው ማለፍ ከበደኝ እንደምንም ካሳለፉኝ በሀላ አልቸቻልኩም ።
ዞርብዬ እሱን እያየሁ ትቼው መሄድ ከበደኝ እንባ ተናነቀኝ በቃ ምንልበላችሁ አቃተኝ ከበደኝ።
ደሞም ከሄድኩ ቀኑን በሙሉ ስለሱ እያሰብኩልጨነቅ እንደሆነ ገባኝ።ከዛም ተመልሼ ወደሱ ሄድኩ።
ምክንያቱም ምን አድርጎ እንደሚጎዳኝ እንኩአን ሳላው ይጎዳሻል ብቻስለተባላኩ መተው አልፈለኩም እናም ቀርቤ ላናግረው ወሰንኩኝ።
ጓደኞቼ መሄዴን ባያምኑበትም ውሳኔዬን ለማክበር ሲሉና ስለሚተማመኑብኝ እራሴን እንድ ጠብቅ አስጠንቅቀውኝ እንድሄድ ፈቀድልኝ ሄድኩ። ነባ አልኩት ልክሲዞር......
ክፍል
ሰባት
ይቀጥላል
1.4K viewssylvie, 15:57