2023-03-14 18:14:19
ምናልባት በዚህ ዓመት ከሚሄዱት ጉዞዎች ከአእምሮዎ የማይጠፋ መንፈሳዊ ቦታ ለመሄድ አስበዋል።ታዲያ
በብዙ ዓመት አንዴ በዕለተ እሁድ የሚውለውን የመስቀለ ኢየሱስን በዓል ለየት ያለ መንፈሳዊ ቦታ ብንወስድዎስ። ነፍስዎን መንፈሳዊ ሀሴትና በረከት ሞልተው መመለስ ከፈለጉና በሚቀጥሉት ዓመታት እለተ እሁድ የማይውለውንና በብዙ ሀሴት ደርሰው የሚመለሱበት መንፈሳዊ ቦታ ጉዞ አዘጋጅተናል ይህ ቦታ እንዠራ መስቀለ ኢየሱስ ገዳም ይባላል።
ከጅሩ መንፈሳዊ ቦታወች እንዠራ መስቀለ ኢየሱስ ገዳም በከፊል እናስተዋውቃችሁ!!!!!!
ሞረትና ጅሩ ወረዳ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን ከሚገኙ ወረዳዎች አንዷነች የወረዳው ርዕስ ከተማ እነዋሪ ስትሆን ከክልሉ ርዕስ ከተማ ከባህርዳር 750 ኪ.ሜ ከመዲናችን ከአዲስ አበባ 195 ኪ.ሜ ከዞኑ ዋና ከተማ ደ/ብረሃን 65 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡
እንዠራ ደብረ ቅዱሳን መስቀል ኢየሱስ ገዳም በሞ/ጅ/ወ በላም ዋሻ ቀበሌ በእንጀራ ጎጥ የሚገኝ ጥንታዊ ገዳም ሲሆን ገዳሙ በ1113 ዓ/ም እንደተመሰረተ የሚነገር ሲሆን ፃድቁ አባት አቡነ ዜና ማርቆስ ደብረ ብስራትን ከመገደማቸው/ገዳም ከመሆኑ/ በፊት ከአቡነ ተክለሐይማኖት ጋር በቦታው ፀልየውበታል፡፡ ገድለ ዜና ማርቆስ ገፅ 36 ምዕራፍ 5 ቁጥር 17/‹‹…ይህ ነገር የተደረገው እንዠራ በሚሏት ሀገር ኢማ ነበር፡፡ ያቺም ለዚህ ለሞረትና ጅሩ ሀገረ ገዥ የላም ዋሻ ማርቢያ ቦታ ናት፡፡››
እንዠራ መስቀል ኢየሱስ ገዳም ከእነዋሪ ከተማ በስተ ሰሜን በግምት 15 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ዋሻ ነው፡፡ ገዳሙ የሚገኘው በደንና በገደል ውስጥ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ በመሆኑ እንኳን ከርቀት ቀርቶ በአቅራቢው ሆኖ መለየት አይቻልም፡፡ አካባቢው ወጣ ገባ ከመሆኑ የተነሳ ከ200 ሜትር ርቀት ላይ ሆኖ እንኳን ደኑን እንጂ ዋሻውን ማየት አይቻልም፡፡
ይህን ቦታ ከሌሎች ቦታዎች ለየት የሚያደርገው በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የሚገኘው ዋሻ ውስጥ ሲሆን ዙሪያውን እንደማንኛውም ቤተ ክርስቲያን ግንብ ሲሆን ጣሪያው ግን ዋሻው እርሱ መሆኑ ነው፡፡
በዚህ ገዳም ውስጥ የተቀበረ አፅመ ቅዱሳን አፈር አይበላውም፡፡ በእንዠራ ደብረ ቅዱሳን መስቀል ኢየሱስ ገዳም ውስጥ የተለያዩ ታሪካዊ መስህቦች የሚገኙ ሲሆን ከነዚህም መካከል፡-
የቅዱሳን አፅሞች
የጊወርጊስ ፈረስ ማሰሪያ የድንጋይ ምሶሶ
የመሬት ውስጥ ጉተራዎች የመሳሰሉት የሚገኝበት ቦታ ነው፡፡
ቦታው በጥንቃቄና በክብር ቢያዝ በተለይ ለሳይንስ ጥናት ምርምር ለተማሪዎች ትልቅ ትምህርትና ምርምር ቦታ እንደሆነ በርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡ በተለይ አንዳንድ ጎብኝዎች ካለማወቅ የተነሳ በተለይም የ5ቱ ሰሞነኞች አፅም ፣የአካባቢው ገዥ የሆነችው የፅዮን ሳምራ እና የአቃቢቷን አፅም በተለያየ ቁስ በመንካት እያበላሹት ስለሚገኝ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡ እንዲሁም የምድር ጎተራው በወቅቱ የአባቶችን ጥበብ የሚገልፅ በመሆኑ ከማድነቅም አልፈን ልንጠብቅ ይገባል፡፡
የጊወርጊስ ፈረስ ማሰሪያ እየተባለ የሚጠራው የድንጋይ ምሶሶ በራሱ ትልቅ ምርምር የሚጠይቅ ቅርስ ነው፡፡ ይህንን ቅርስ ለመጠበቅ ደግሞ የሁሉም አካል ድርሻ የራሱ የሆነ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው፡፡
የጊዮርጊስ ፈረስ ማሰሪያ
ያንን ህዝቡ የሚያመልኩበትን ዘንዶ ከገደሉ በኋላ አቡነ ዜና ማርቆስና ፣ አቡነ ተክለሃይማኖት ህዝቡን አስተምረው አጥምቀው ክርስትያን አድርገውታል፡፡ ›› (ምንጭ ገድለ ዜና ማርቆስ 9ኛ ተአምር ገፅ 234 ና 235) እንዲሁም ፅዮን ሳምራ ቤተ ክርስቲያን ካሳነፀች በኋላ ያነፀውን አሽከሯን ይህንን ሙያ እዚህ እኔጋ አትቀመጥልኝም በማለት ቀኝ እጁን አስቆርጣዋለች፡፡
የድንጋይ ምሶሶ
አቃቢቷ በጥንቃቄ መገበሪያውን ባለማዘጋጀታቸው እና ከ5ቱ ሰሞነኞች ጋር በመመሳጠራቸው አቃቢቷ እስከ ወንፊቷና እስከ ሰፌዷ በአለችበት ደርቃ ቀርታለች፡፡
አምስቱ ሰሞነኞችና አቃቢቷ እስከ ወንፊቷና እስከ ሰፌዷ
እነዚሁ 5ቱ ሰሞነኞችና ፅዮን ሳምራን አፅማቸው
366 views15:14