2022-07-20 08:52:05
#ጊዜዉ_አልቋል_ሁላችሁም_አብራችሁን_ሥሩ?
“ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።”
— ማቴዎስ 24፥14
ኢትዮጵያ ዉስጥ ካለዉ 120.ሚሊዮን ሕዝብ ዉስጥ ዳግም የተወለደ ክርስቲያን የሚባለዉ 30.ሚሊዮን ነዉ፤ ልብ በሉ ከዚህ በፊት የተመዘገበዉን እና ወደ አለም የተመለሰዉን አማኝ ጨምሬ ነዉ 30ሚሊዮን ያልኳችሁ። በዚህ የህዝብ ቁጥር እንኳን ብንሄድ 90 ሚሊዮን የሚሆነዉ ክርስቶስን ባለማመንና ዳግም ባለመወለድ ከእግዚአብሔር ቁጣ ስር ነዉ፥ ንስሃ ገብቶ ካልዳነ መጨረሻዉ ገሃነም ነዉ። ስለዚህ እኛም በሚጠፉት ሰዎች ደም እንዳንጠየቅ በልቤ ያለዉን ሸክም ወደ እናንተ አመጣለዉ። ማናችንም ብንሆን ወንጌል ካልተናገርን እና ያለንን ሁሉ ለወንጌል የማናዉል ከሆነ በጌታ ፊት ከተጠያቂነት አንድንም።
“ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም፤ ግድ ደርሶብኝ ነውና፤ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 9፥16
ዛሬ ጥሪ የማደርግላችሁ ሰዎች ሁለት ጊዜ እንድታስቡ ሳይሆን አንብባችሁ ምላሽ እንድትሰጡኝ ነዉ። እጅግ ብዙ ሕዝብ እግዚአብሔር እንደሚሰጠን አዉቃለዉ። ከዚህም በፊት:_ ጊዜዉ አልቋል ምን ትጠብቃላችሁ ብለን ባደረግነዉ ዘመቻ ሚሊዮኖችን ደርሰን ብዙ ሺዎችን ወደ እግዚአብሔር መንግስት አምጥተናል። አሁን ግን በኢትዮጵያና በመላዉ አለም ያላችሁ ሰዎች በተሰጣችሁ የአገልግሎት ፀጋ፣ በገንዘባችሁ፣ በእዉቀታችሁ፣ በቁሳቁስ እጃችሁ ላይ ባለዉና ሁሉ አብራችሁን እንድታገለግሉ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ። እግዚአብሔር የሰጣችሁን እድልና ጊዜ ተጠቀሙ።
#ኢየሱስ_ክርስቶስ_በክብር_ይመጣል።
ጌታን የምትወዱ እና ባላችሁ ነገር ሁሉ ማገልገል የምትፈልጉ ወንድሞችና እህቶች #ብቻ አብራችሁን ለማገልገል ፃፉልኝ።
መልካም ቀን። ሐምሌ 13/11/2014ዓ.ም፤ “የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።”
— 2ኛ ቆሮ 13፥14
#የእግዚአብሔር_አገልጋይ_ማስረሻ_በላይ
መልዕክቱን ለሌሎች አድርሱልኝ።
697 viewsМαѕяєѕнα вєʝαу, 05:52