Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ምኩራብ ቤተክርስቲያን/ SYNAGOGUE OF GOD CHURCH/ ⭐ ሲኤምሲ አጥቢያ ⭐

የቴሌግራም ቻናል አርማ masreshamulumebet — የእግዚአብሔር ምኩራብ ቤተክርስቲያን/ SYNAGOGUE OF GOD CHURCH/ ⭐ ሲኤምሲ አጥቢያ ⭐
የቴሌግራም ቻናል አርማ masreshamulumebet — የእግዚአብሔር ምኩራብ ቤተክርስቲያን/ SYNAGOGUE OF GOD CHURCH/ ⭐ ሲኤምሲ አጥቢያ ⭐
የሰርጥ አድራሻ: @masreshamulumebet
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.97K
የሰርጥ መግለጫ

የእግዚአብሔር ምኩራብ ቤተክርስቲያን
SYNAGOGUE OF GOD CHURCH
⛪⭐ የሲኤምሲ"መሪ" አጥቢያ ቤተክርስቲያን ⭐⛪
🌎 WORLD WIDE FAMILY GROUP 🌎
“እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።”
— ኤፌሶን 5፥27

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-31 08:29:06
#ማደግ_ግዴታችሁ_ነዉ

የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስ መልክ በዕድገታችሁ ልክ ይገለጣል። "የጌታን መልክ በመወለድ ትካፈሉታላችሁ በዕድገት ትገልጡታላችሁ።" በጌታ ያልተወለደ ዘሩ እንደማይገኝበት ሁሉ እንዲሁ ያላደረገ ደግሞ መልኩ አይገለጥበትም። እግዚአብሔር በመወለዳችሁ ደስ ይለዋል። በማደጋችሁ ግን ይከብራል። መፅሐፍ ቅዱስ በሉቃስ 15. ላይ እንደሚነገረን የጠፋዉ ልጅ ሲገኝ በሰማይ ታላቅ ደስታ ይሆናል ይለናል። በዮሐንስ ወንጌል 15. መሠረት ግን እግዚአብሔር ይከብራል ብሎ ከማደግና ብዙ ፍሬ ከማፍራት ጋር ያይዘዋል።

“ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራል።”
— ዮሐንስ 15፥8

ስለዚህ መወለዳችሁ ለእግዚአብሔር ደስታ እንጂ ለእግዚአብሔር ክብር አይሆንም። እግዚአብሔር ከእናንተ ህይወት ክብር የሚያገኘው ስትወለዱ ሳይሆን ስታድጉ ነው። "የክርስትና ውሃ ልክ ወይም መለኪያው ፀጋ ወይም ቅባት ሳይሆን የልጁ መልክ ነው። በእግዚአብሔር ፊት የምትለኩት ባላችሁ ፀጋ ወይም ቅባት ሳይሆን ምን ያህል የልጁን መልክ ገልጣችኃል በሚለው ነዉ።" ቅባት የእግዚአብሔርን ሀይል ይገልጣል ዕደገት የልጁን መልክ ይገልጣል። ቅባት በእግዚአብሔር የመቀባት ውጤት ነው መልክ ግን ክርስቶስን የመኖር ውጤት ነው። የትኛውም ፀጋና ቅባት ክርስቶስን ለመምሰላችሁ ዋስትና ሊሆናችሁ አይችልም። የልጁን መልክ የሚያመጣው የእግዚአብሔር ህይወት በመኖር የመንፈስ ፍሬን በማፍራት ነዉ። ይህ ደግሞ ራስን እግዚአብሔርን መምሰል በማስለመድ የሚገኝ ውጤት ነዉ።

“ነገር ግን ለዚህ ዓለም ከሚመችና የአሮጊቶችን ሴቶች ጨዋታ ከሚመስለው ተረት ራቅ። እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥7

#የእግዚአብሔር_አገልጋይ_ማስረሻ_በላይ
መልዕክቱን ለሌሎች አድርሱልኝ።
355 viewsМαѕяєѕнα вєʝαу, 05:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 06:57:28 “ደቀ መዛሙርቱም በባሕር ላይ ሲሄድ ባዩት ጊዜ፦ ምትሐት ነው ብለው ታወኩ በፍርሃትም ጮኹ።”
— ማቴዎስ 14፥26
544 viewsМαѕяєѕнα вєʝαу, 03:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 06:57:28 ሠላም የተወደዳችሁ ቤተሰቦቼ እንዴት አደራችሁ ዋላችሉ አመሻችሁ?
538 viewsМαѕяєѕнα вєʝαу, 03:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 09:48:26
#ህይወት_ያለበት_ድንቅ_መዝሙር_ነዉ_ስሙት።
እንዲከተላችሁ አስቀድሙ!

በእግዚአብሔር መንግስት የሚያስፈልጋችሁ ነገር ይከተላችኋል እንጂ አትከተሉትም። ክርስትና መከተል ሳይሆን ማስቀደም ነው። የእግዚአብሔርን መንግስት እስካስቀደማችሁ ድረስ ሊከተላችሁ የተገባ ነገር በሙሉ ይከተላችኋል። ምድራዊ ነገር ሲከተላችሁ በረከት ነው። ስትከተሉት እርግማን ነው። ቤተክርስቲያን ዉስጥ ሆኖ ላለመረገም የህይወታችሁ ዋና ለሚሆነዉ ፅድቅና መንግስቱ ቅድሚያ ስጡ።

“ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።ማቴዎስ 6፥33

መልካም ቀን። ሐምሌ 19/11/2014ዓ.ም፤ “የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።”
— 2ኛ ቆሮ 13፥14

#የእግዚአብሔር_አገልጋይ_ማስረሻ_በላይ
መልዕክቱን ለሌሎች አድርሱልኝ።
626 viewsМαѕяєѕнα вєʝαу, 06:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 07:56:30 በዚህ ማለዳ ባረኳችሁ፤ ከየትኛዉም እስራት እግዚአብሔር ዛሬና አሁን ይፍታችሁ በኢየሱስ ስም።
ሀይልን ይጨምርላችሁ፣ የሚያቆማችሁ አይኑር፣ ራሳችሁን እንድትዘጉ የሚያደርግ የሚጥር አይኑር፣ መንገዶቻችሁን ለማዘጋት፤ ለማስቀረት፤ ለማብረድ፤ ለማቀዝቀዝ፤ ለማዘግየት፤ ለማስቀረት ማንም እናንተን አይቻል በጌታ በኢየሱስ ስም። እግዚአብሔር ያሻግራችሁ፣ እግዚአብሔር ከጤንነትን ፈተና ያሻግራችሁ፣ ከኑሮ ተግዳሮት ያሻግራችሁ፣ ከተቃዋሚዎች ሁኔታ ያሻግራችሁ እግዚአብሔር በአምላኬ ቅጥሩን ያዘልላችሁ፣ ወደ ሰፊ ሜዳ ያውጣችሁ፣ እግዚአብሔር ሀይል ይስጣችሁ በጌታ በኢየሱስ ስም። በተከፈተላችሁ በር መውጣትና መግባት ይሁንላችሁ፣ የተባረኩ ቀኖችን ይጨምርላችሁ፣ የእግዚአብሔር ደስታ አሁንም በእናንተ በኩል ይፈጸም። ሽንፈትን፤ ድካምን፤ ዝለትን፤ ስንፍናን፤ ተግዳሮትን እግዚአብሔር ከፊታችሁ ይጣልላችሁ፤ እነዚህን ተሻግራችሁ ሂዱ፣ የተባረከ ቀንና ዘመን ይሁንላችሁ። መልካም ቀን/ለሊት ተባረኩ።
533 viewsМαѕяєѕнα вєʝαу, 04:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 15:26:37
#ለምትወዱኝና_ለምታከብሩኝ_ጥሪ_አለኝ።
የህክምና ባለሙያዎችና የግል ህክምና ማዕከል ያላችሁ ፃፉልኝ።

“ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፤ እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል። እግዚአብሔር ይጠብቀዋል፥ ሕያውም ያደርገዋል፥ በምድር ላይም ያስመሰግነዋል፥ በጠላቶቹም እጅ አያሳልፈውም። እግዚአብሔር በደዌው አልጋ ሳለ ይረዳዋል፤ መኝታውን ሁሉ በበሽታው ጊዜ ያነጥፍለታል።”
— መዝሙር 41፥1-3

አሁን በሰአታት ልዩነት ከአቶ ሳምሶን ልጠፋ በኃላ ከደብረዘይት አንድ የእርዳታ ጥሪ ደርሶኛል። በስልክ ያገናኙኝ የህፃኗን አባት ነበር፤ ቪዲዮን ለማየት እጅግ ይጨንቃል ያለማቋረጥ ልጅቷ ታለቅሳለች፣ ትጮሃለች አስጨናቂ ድምፅ ከዉስጥ ይሰማል። ሕይወት ቶላ ትባላለች 2 ዓመት ከ6 ነው የተሰቃየችዉ፤ አቅማቸው ስላልቻለ ከሆስፒታል አዉጥተዉ አሁን ቤት እያለቀሱ ይገኛሉ። እባካችሁ ይህን ቪድዮ ሼር በማድረግ ሕይወትን ቶላን እንታደጋት። በዉስጥ መስመር ፃፉልኝና የምትልኩልኝን ገንዘብ ሰብስበን ከወዳጆቼ ጋር አንዱን ቀን ወደ ደብረዘይት እንጓዛለን፤ አብራችሁኝ ለመሄድና ለማገዝ የምትፈልጉም ፃፉልኝ። በሉ አሁን ቶሎ ቶሎ በሞባይል ባንኪንግ እና አጠገባችሁ ባለዉ የባንክ ቅርንጫፍ በመሄድ ላኩልኝ፤ ያስገባችሁበትን የባንክ ደረሰኝ እና የሞባይል መልዕክት Screenshots በማንሳት ላኩልኝ። መልካም ሰንበት ይሁንላችሁ።

COMMERICAL BANK OF ETHIOPIA:_ 1000214444147

መልካም ሰንበት። ሐምሌ 17/11/2014ዓ.ም፤ “የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።”
— 2ኛ ቆሮ 13፥14

#የእግዚአብሔር_አገልጋይ_ማስረሻ_በላይ
መልዕክቱን ለሌሎች አድርሱልኝ።
521 viewsМαѕяєѕнα вєʝαу, 12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 15:26:14
#እግዚአብሔር_ምህረቱን_ያብዛልሽ።
እግዚአብሔር ጣልቃ ገብቶ ያሳርፋችሁ፤ ፊቱንም እንደገና በላያችሁ ይመልስ።

በእግዚአብሔር መሃሪነትና በእናንተ ወዳጆቻችን ርብርብ ለብዙ ጊዜ በኮራያ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ ሲደረግላት የቆየችው ታዳጊዋ በረከት ሳምሶንን ይዘው እናት"እናት" እና አባት"ሳምሶን" ወደ ኒው ደልሂ ደርሰዋል። እግዚአብሔር በዚያ በሚገኙ ኃኪሞች ደግሮ አይምሮና እጃቸዉን ተጠቅሞ ተዓምራት እንዲያደርግ ፀልዩላቸው።

https://gofund.me/33bbc527

1000268540346 (ንግድ ባንክ)
ወንጌላዊ ሳምሶን በቀለ ስጦታው/ወላጅ አባቷ/
+251911531893
+251911843173

ከዚህ በፊት የተለጠፈዉ የእርዳታ ጥሪ
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1056111501697518&id=100018960344574&sfnsn=mo

መልካም ሰንበት። ሐምሌ 17/11/2014ዓ.ም፤ “የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።”
— 2ኛ ቆሮ 13፥14

#የእግዚአብሔር_አገልጋይ_ማስረሻ_በላይ
መልዕክቱን ለሌሎች አድርሱልኝ።
435 viewsМαѕяєѕнα вєʝαу, 12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 22:09:47 “በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤”
— ኤፌሶን 6፥18
482 viewsМαѕяєѕнα вєʝαу, 19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ