Get Mystery Box with random crypto!

4) የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሕዝባቸውና የቁርጥ ቀን ባለውለታቸው በሆነው ልዩ ኃይል ላይ የሚወ | Christian Tadele Tsegaye

4) የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሕዝባቸውና የቁርጥ ቀን ባለውለታቸው በሆነው ልዩ ኃይል ላይ የሚወስዱትን እርምጃ እንዲያቆሙና ወደ ካምፓቸው እንዲመለሱ፤ በተለይም የአማራ ልዩ ኃይል አባላት የአገር አንድነት የመጨረሻ ምሽግ ከሆነው የመከላከያ ኃይል ጋር ወደ ግጭት የሚያስገቡ ጉዳዮችን በማስወገድ ተረጋግተውና አንድነታቸውን ጠብቀው በካምፓቸው እንዲሰበሰቡ፤ የአማራ ሕዝብ ለልዩ ኃይሉ ተገቢውን ድጋፍ ሁሉ እንዲያደርግ፤ መላው ኢትዮጵያውያንም የብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴን ኢሕገመንግስታዊ አገር አፍራሽ እርምጃ በአንድነት እንድታወግዙ ጥሪያቸንን እናቀርባለን።

5) የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ልኂቃን፣ ሚዲያዎችና የማኅበረሰብ አንቂዎች ግጭት አባባሽ ከሆኑ ጉዳዮች በመታቀብ የገዥውን ፓርቲ ፋሽስታዊ እርምጃዎች በመርሕና ሕግ በመመርኮዝ በጽናት ትታገሉ ዘንድ ከአደራ ጭምር ጥሪያችንን እናቀርባለን።

6) የዓለምአቀፍና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ የብልጽግና ፓርቲ ከገባበት አገርን የማፍረስ እኩይ ተልእኮው በመታቀብ ሕግ አክብሮ እንዲንቀሳቀስ፤ በየጊዜው ግጭቶችን እየጠመቀ በንፁኃን ላይ የሚያደርሰውን የዘር ፍጅትና ማንነት ተኮር ጅምላ ጭፍጨፋዎች እንዲያቆም፤ የሰብአዊ መብቶችን አክብሮ የመንቀሳቀስ ዓለምአቀፋዊ መርሆ እንዲያከብር አስፈላጊ እርምጃዎችን ሁሉ በመውሰድ ታሪካዊ ኃላፊነታችሁን ትወጡ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን። ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ዓለምአቀፍ ማኅበረሰቡ በሩዋንዳ የዘር ፍጅት የፈፀመውን ታሪካዊ ስህተት እንደሚደግም ማስጠንቀቅ እንፈልጋለን።


ሚያዝያ 03፣2015 ዓ/ም
አዲስ አበባ፥ ሸዋ፣ ኢትዮጵያ