በሰኔ ወር የማንችስተር ዩናይትድ ስራ አስኪያጅ ሪቻርድ አርኖልድ ከደጋፊዎች ጋር ባደረገው ስብሰባ ማንቸስተር ዩናይትድ ለዝውውሮች 200 ሚሊየን ፓውንድ በጀት እንዳለው እና ይህንንም በጀት ተጨዋቾችን ለማምጣት እንደሚጠቀምበት አሳውቆ የነበረ ሲሆን አሁን ላይም ማንቸስተር ዩናይትድ በዝውውር መስኮቱ ያወጣው ጠቅላላ ወጪ 201 ሚሊየን ፓውንድ ደርሷል። ማንችስተር ዩናይትድ በኤድ ዉድዋርድ ከአስር አመታት የዝርክርክ ስራዎች በኋላ ላይ አሁን ቃሉን የሚጠብቅ እና ለደጋፊዎቹ እውነቱን የሚናገር ስራ አስኪያጅ ያለን ይመስላችኋል? አሁንም #Glazers_Out እንዳይረሳ! @Kareem_Abuki @man_united_ethio_fans 24.2K views𝐊𝐀𝐑𝐄𝐄𝐌 𝐀𝐁𝐔𝐊𝐈 , 19:22