Get Mystery Box with random crypto!

ማዕዶት ዘተዋሕዶ

የቴሌግራም ቻናል አርማ maedote — ማዕዶት ዘተዋሕዶ
የቴሌግራም ቻናል አርማ maedote — ማዕዶት ዘተዋሕዶ
የሰርጥ አድራሻ: @maedote
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.87K
የሰርጥ መግለጫ

የትንሣኤ እሑድ ማግሥት ጌታ
ክርስቶስ በትንሣኤው ምዕመናንን ከሞት ወደ ሕይወት ያሻገረበት ቀን የትንሣኤው ማሳሰቢያ ማዕዶት ይባላል። ......በዚህም channel ወደ ሕይወት ይሻገሩበት

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-04 21:41:51 ወንጌሉን እንጀምራለን

" በመጀመሪያው ቃል ነበር " ( ዮሐ ፩:፩)

እዚህ ምዕራፍ ላይ ትንሽ እንቆያለን መሰረታዊ ምዕራፍ ስለሆነ ጊዜ ወስደን በተቻለ አቅም ሳይበዛ እንማማራለን

#በመጀመሪያው - መጀመሪያ የሚለውን ቃል ስናይ መነሻ ያለው መጀመሪያ አለ ፤ መነሻ የሌለው መጀመሪያ በሁለት ይከፈላል
= ጥንት የሌለው መጀመሪያ ( ዘፍ 1:1 )
=መነሻ ያለው መጀመሪያ ( ዘፍ 1:1)

“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።” (ዘፍጥረት 1፥1 )

ዮሐንስ ወንጌል ላይ ያለው መጀመሪያ መጀመሪያ የሌለው መጀመሪያ መሆኑን የምናውቀው በመጀመሪያው ቃል ነበር ይላል ኦሪት ዘፍጥረት ላይ ያለው መጀመሪያ መነሻ ያለው መሆኑን የምናውቀው በመጀመሪያ ሰማይ እና ምድር ተፈጠሩ ብሎ ይነሳል ነበርና ተፈጠሩ ትልቅ ልዩነት አለው።

ስለዚህ በመጀመሪያ የምትለው ቃል ጥንት የሌለው መጀመሪያ መሆኑን ያስረዳል።

ቀጣይ በመጀመሪያ ሳይሆን የሚለው በመጀመሪያው ነው ለምን "ው" የምትለው ቃል ተጠቀመ ለምን ??? እንመለስበታለን
457 viewsmuluken Ayele, 18:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 11:37:20
ሌላ የምንመለከተው ልክ እንደ ሄኖክ ኤልያስ ቅዱስ ዮሐንስ ሞትን ያልቀመሰ እንደሆነ ይነገራል ይህውም በወንጌል ላይ

" በምን ዓይነት ሞት እግዚአብሔርን ያከብር ዘንድ እንዳለው ሲያመለክት ይህን አለ። ይህንም ብሎ፦ ተከተለኝ አለው። ጴጥሮስም ዘወር ብሎ #ኢየሱስ #ይወደው #የነበረውን #ደቀ #መዝሙር #ሲከተለው #አየ፤ እርሱም ደግሞ በእራት ጊዜ በደረቱ ተጠግቶ፦ ጌታ ሆይ፥ አሳልፎ የሚሰጥህ ማን ነው? ያለው ነበረ። ጴጥሮስም ይህን አይቶ ኢየሱስን፦ ጌታ ሆይ፥ ይህስ እንዴት ይሆናል? አለው። ኢየሱስም፦ #እስክመጣ #ድረስ #ይኖር ዘንድ ብወድስ፥ ምን አግዶህ? አንተ ተከተለኝ አለው። ስለዚህ፦ ያ ደቀ መዝሙር አይሞትም የሚለው ይህ ነገር ወደ ወንድሞች ወጣ፤ ነገር ግን ኢየሱስ፦ እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ብወድስ ምን አግዶህ? አለው እንጂ አይሞትም አላለውም። " ( ዮሐንስ 21 ፤ 18-24 )

በግልጽ የሚያሳየው ያ ደቀመዝሙር ሞትን ሳይሞት ክርስቶስ እስኪመጣ ድረስ እንደሚቆይ ምን አግዶ እንዳለው ለቅዱስ ጴጥሮስ እንመለከታለን።

ይህ ደቀ መዝሙር ( ቅዱስ ዮሐንስ) በምድር ላይ ሁለት ዘመናት ቆይቷል በሐዋርያት( Apostolic) እና በድኅረ ሐዋርያት ( Post Apostolic ) በዙህም የቅርብ ዘመን የሐሰት ትምህርቶችን ተመልክቷል።
531 viewsmuluken Ayele, edited  08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 19:24:47
፬) አቡቀለምሲስ ይባላል ( ባለ ራእይ ማለት ነው )
" ዮሐንስ አቡቀለምሲስ ዘረፈቀ ውስተ ሕፃኑ ለኢየሱስ ፤ በጌታችን አጠገብ የሚቀመጥ አቡቀለምሲስ ዮሐንስ " ( ድጓ ገጽ 192 )
የዮሐንስ ራእይን ስለፃፈ ባለ ራእይ ተባለ


ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊው መጽሐፍት
1) ወንጌል ( በ90 ዓ.ም በፍጥሞን ደሴት አንድም በሃገረ ስብከቱ እንደተፃፈ ይታመናል )

ከሌሎች ወንጌላውያን ዘግይቶ እንደፃፈ የመጽሐፍ ማስረጃዎች አሉ ከነዚህም አንዱን ለመጥቀስ ያህል
" ኢየሱስም ከመቅደስ ወጥቶ ሄደ፥ ደቀ መዛሙርቱም የመቅደሱን ግንቦች ሊያሳዩት ቀረቡ። እርሱ ግን መልሶ፦ ይህን ሁሉ ታያላችሁን? እውነት እላችኋለሁ፥ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አላቸው። " ( ማቴ 24:1-2 ፤ ማር 13፣1-2 ፤ ሉቃ 21:5-7 ) ሦስቱም ወንጌላውያን ይህንን ነገር ጽፈዋል ዮሐንስ ወንጌል ላይ ግን አናገኘውም ምክንያቱም ቤተ መቅደሱ የፈረሰው በ70 ዓ.ም ነው ዮሐንስ ወንጌሉን የጻፈው በ90ዓ.ም ገደማ ከፈረሰ በሃላ ተብሎ እንደማስረጃ ይጠቀሳል።

2) መልእክታት
-፩ኛ ዮሐንስ መልእክት የጻፈው ለነበሩ ሕዝቦች ነው።
-፪ኛ መልእክቱን የጻፈው ከደቀመዛሙርቱ አንብሮስ ጋር ሆኖ ወደ ሃይማኖት ለመለሳት ለእመቤት ሮምና ነውና
-፫ኛ መልእክት የጻፈው ለክርስትያኖች በመርዳት ይታወቅ ለነበረው ለጋይዮስ ነው።

3) ራእይ ( በፍጥሞን ደሴት በግዞት ላይ በ97ዓ.ም መጨረሻ ገደማ የተጻፈ መጽሐፍ ነው)

4) 14ቱ የቅዳሴ መጽሐፍ ውስጥ ቅዳሴ ወልደ ነጎድጓድን ጽፉል።
571 viewsmuluken Ayele, edited  16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 17:22:51 ፪) ወልደ ነጎድጓድ የነጎድጓድ ልጆች ( ቦአኔርጌስ )

ዮሐንስ ያዕቆብ ወንድሙ የሰማርያ ሰዎች በእሳት እንዲጠፉ ተመኝተው በዚህ ዓይነት የችኩልነት ስሜት የተነሳ በዚህ ስያሜ የሰየማቸው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
“የዘብዴዎስንም ልጅ ያዕቆብን የያዕቆብንም ወንድም ዮሐንስን ቦአኔርጌስ ብሎ ሰየማቸው፥ የነጎድጓድ ልጆች ማለት ነው፤”
— ማርቆስ 3፥17
፫) ታዎጎሎስ .....ቴዎጎሎስ

በግዕዝ ነባቤ አምላክ ፣ ነባቤ መለኮት ይባላል በአማርኛ የመለኮት ነገር የተናገረ ማለት ነው። በመጀመሪያው ቃል ነበር። ( ዮሐ ፩፤፩) ብሎ የወልድን መለኮታዊ ህልውና የወልድን ቀዳማዊነቱን እና የአለም ፈጣሪ መሆኑን ገልጦ ስለተናገረ ይህ ስያሜ ተሰጠው።

፬) አቡቀለምሲስ ይባላል ( ባለ ራእይ ማለት ነው )
በቀጣይ እንመለከታለን
463 viewsmuluken Ayele, edited  14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 17:12:06
ቅዱስ ዮሐንስ ብዙ ስሞች አሉት ከነዚህ መሐል
፩) ፍቁረ እግዚእ ( የጌታችን ወዳጅ ፤ ጌታ ይወደው የነበረ )

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ለምን ከሐዋርያት ለይቶ ጌታ ይወደው የነበረ ሌሎቹ አይወዳቸውም ማለት ነው ? ለሚለው ምላሽ ሲሰጥ " ፀሐይ ልትገባ የምትችለው በአንድ ቤት ውስጥ በተከፈተላት ቀዳዳ መጠን ነው ዮሐንስ ወንጌላዊው ሌሎቹን በመጠኑ ጣርያውን ሲከፍቱ ዮሐንስ ፀሐይ የተባለው ክርስቶስን የተቀበለው በሙሉ ልቡ ( ሙሉ ጣርያውን ነድሎ ) ነው ለዚያ ነው ጌታ ይወደው የነበረ የተባለው " ብሎ ፈቶታል።
477 viewsmuluken Ayele, 14:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 18:03:27
መጽሐፍት ( ቅዱስ መጽሐፍት ) በእግዚአብሔር መንፈስ ነው የተጻፉት መጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ ያስፈልጋቸዋል

የቅዱስ ዮሐንስ ጥንተ ነገሩ እንደምንድን ነው ቢሉ #አባቱ #ዘብዴዎስ ባለ ጠጋም ነበር ( ማር 16 : 1 ) #ከቤተ #ይሁዳ ይወለዳል እናቱ #ሰሎሜ ትባላለች ( ማቴ 27:56 ) እርሷም #ከቤተ #ለዊ ናት።

ቅዱስ ያሬድ " ዮሐንስ ድንግል ሆይ ለምንልን አማልደን የመለኮት ወንጌልን ሰበክህ #አባትህ #ከቤተ #መንግስት ነው #እናትህም #ከቤተ-ክህነት ናት ስለዚህ አቡቀለምሲስ ተባልክ " ድጓ ገጽ 192 ። ....በድጋሚ
ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቅዳሴ መግቢያ ላይም " ዮሐንስ #ከቤተመንግሥት #ከቤተ #ክህነት #ይወለዳል " ብለው ጽፈዋል።
ዮሐንስም ከአባቱ ጋርም ይሰራ ነበር። ማርቆስ 1 ላይ ያለውን ጥቅስ ብንመለከት ግልጽ ያደርገዋል -

" ከዚያም ጥቂት እልፍ ብሎ #የዘብዴዎስን #ልጅ #ያዕቆብን #ወንድሙንም #ዮሐንስን ደግሞ በታንኳ ላይ መረባቸውን ሲያበጁ አየ። ወዲያውም ጠራቸው አባታቸውንም #ዘብዴዎስን #ከሞያተኞቹ ጋር በታንኳ ላይ ትተው ተከትለውት ሄዱ። " ማር 1: 16-17

የቅዱስ ዮሐንስ አባት ዘብዴዎስ ሞያተኞች እንዳሉት ማለትም ቀጥሮ የሚያሰራ የሚያስተዳድር ሰው እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። እዚህ ጋር ወንድሙ ሐዋርያት የተቆጠረው ከዮሐንስ ጋር ለዮሐንስ መጥምቅ ደቀ መዝሙር የነበረ " እነሆ የእግዚአብሔር በግ" ብሎ ሲናገር ሰምተው ጌታችንን የተከተሉት ከሁለቱ ደቀ መዝሙር አንዱ ያዕቆብ ይባላል። በንጉሥ ሄሮድስ እጅ የተገደለው ያዕቆብ ነው።
“የዮሐንስንም ወንድም #ያዕቆብን #በሰይፍ #ገደለው።”
— ሐዋርያት 12፥2
ተብሎ ተጽፏል።

ቅዱስ ዮሐንስ የጻፍቸው መጽሐፍት እና ስሞች በቀጣይ እንመለስበታለን።
586 viewsmuluken Ayele, 15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 21:03:51
“ይደልዎ ለዘያነብብ ቅድመ ይዝክር ስሞ ለበዓለ መጽሐፍ ወእምዝ ያንብብ ወይምሀር፤ የተጻፈን ነገር ለሚያነብ ሰው የተጻፈውን ጉዳይ ከማንበቡ በፊት የጸሓፊውን ማንነት ይወቅ፣ ካወቀ በኋላ አንብቦ ያነበበውን ያስተምር” ይላል። የጸሓፊውን ማንነት ማወቅ የጽሑፉን ስሜት እንድንረዳው ይረዳናል።

( ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተግሣጽ 8 ገጽ 99 )

ስለዚህ ወንጌሉን ከመጀመሪያችን በፊት ስለ ቅዱስ ዮሐንስ
1) ቅዱስ ዮሐንስ ማን ነው ?
2) የቅዱስ ዮሐንስ መጠሪያ ስሞች ?
3) የማን ደቀ መዛሙር ነበረ
4) አባቱ እና እናቱ ማን ይባላሉ ወንድሙስ ?
5) የጻፍቸው መጽሐፍት

የሚለውን እንመለከታለን።
601 viewsmuluken Ayele, edited  18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 19:17:14
የዮሐንስ ወንጌል ትርጓሜ

ክፍል 1) "ጸሐፊውን ማወቅ ( ስለ ጸሐፊው ) "
582 viewsmuluken Ayele, 16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 13:10:49 የዮሐንስ ወንጌል ትርጓሜ እግዚአብሔር በገለጠልን መንገድ ብንማማር ለመማር ፍላጎት ያላቹ ምልክቷን ተጫኑ
635 viewsmuluken Ayele, 10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 14:22:24
720 viewsmuluken Ayele, 11:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ