ጎደቤ ብሔራዊ ፓርክ የተፈጥሮን ሚዛንን ከሚጠብቁ ተፈጥሮአዊ ፀጋዎች መካከል እፅዋት ዋነኞቹ ናቸው።በሀገራችን ከሰሃራ በረሃ የሚመጣውን ሞቃታማ አየር ከሚገቱ ና በደን የተሸፈኑ አካባቢዎች በሀገራችን ሰሜናዊ ክፍል የሚገኘው የጎደቤ ብሔራዊ ፓርክ አንዱ ነው። ፓርኩ 18987 ሄክታር የሚሸፍን ሲሆን ውብ ከሆነ የመልካምድር አቀማመጡና እንደ ዘብ ከቆሙ ተራራዎች ልዩ ውበት ተችሮታል። በውስጡ ከ27 በላይ የዱር እንስሳት ከ57 በላይ የወፍ ዝርያዎች እንዲሁም እየተመናመነ የመጣውን የእጣን ዛፍ ለቅርፃ ቅርፅ መስሪያ አስተዋፅኦ ያለውን የቆላ ቀርከሃ ና ከ81 በላይ እፅዋትን የያዘ ነው። @LWEQESH_Events 130 viewsሚክሎል, 17:47