በትግራይ ክልል የንግድ ባዛር ሊካሄድ ነው የትግራይ ክልልን የንግድ እንቅስቃሴ ማነቃቃት አላማ ያደረገ የንግድ ባዛር መቀሌን ጨምሮ በአራት የክልሉ ከተሞች እንደሚካሄድ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። ባዛሩ ሚያዚያ 21 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በመቀሌ ከተማ በይፋ እንደሚከፈትና በውቅሮ፣ አዲግራትና ማይጨው ከተሞችም እንደሚካሄድ ተመላክቷል። ከባዛሩ በተጨማሪ የፓናል ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል። @Leyu_News @Leyu_News 2.9K viewsedited 18:30