ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከረባቸዉ አምስቱ ችንካሮች (ሚስማሮች) ስም፦ #1ኛ ሳዶር #2ኛ አላዶር #3ኛ ዳናት #4ኛ አዴራ #5ኛ ሮዳስ አምስቱ የእመቤታችን ኃዘናት፦ #1ኛ ከአምስቱ አንዱ አይሁድ እንዲገድሉክ በቤተ መቅደስ ስምዖን ትንቢት በተናገረ ጊዜ ነዉ።ሉቃ 2÷34 #2ኛ ሁለተኛዉም ሦስት ቀን በቤተ መቅደስ ባጣሁህ ጊዜ ነዉ።ሉቃ 2÷41 #3ኛ ሦስተኛዉም እጅህን እግርህን አስረዉ በጲላጦስ አደባባይ የገረፉህን ግርፋት ባሰብኩ ጊዜ ነዉ።ዮሐ19÷1 #4ኛ አራተኛዉም በዕለተ አርብ እራቆትህን ቸንክረዉ በሁለት ወንበዴዎች መካከል እንደሰቀልኩ ባሰብኩ ጊዜ ነዉ አለችዉ። ዮሐ19÷17 #5ኛ አምስተኛዉም ወደ ሐዲስ መቃብር ዉስጥ እንዳወረዱህ ባሰብኩ ጊዜ ነዉ።ዮሐ 19÷38 ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈፀሙ 7ቱ ተአምራት፦ #1ኛ ፀሐይ ጨልሟል #2ኛ ጨረቃ ደም ሆነ #3ኛ ከዋክብት እረገፉ #4ኛ ዓለቶች ተሰነጠቁ #5ኛ መቃብር ተከፈቱ #6ኛ ሙታን ተነሱ #7ኛ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለሁለት ተቀደደ ሰባቱ የመስቀል ላይ ንግግሮች፦ #1ኛ አምላኬ አምላኬ ለምን ተዉከኝ።ማቴ 27÷46 #2ኛ አባት ሆይ የሚያደርጉት አያዉቁምና ይቅር በላቸዉ። ሉቃ 23÷34 #3ኛ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር እንድትኖር በእዉነት እነግረሃለሁ። ሉቃ 23÷43 #4ኛ እነሆ ልጅሽ አነዃት እናትህ።ዮሐ 19÷26 #5ኛ ተጠማሁ።ዮሐ 19÷28 #6ኛ አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ።ሉቃ 23÷46 #7ኛ የተፃፈ ሁሉ ደረሰ ተፈፀመ አለ።ዮሐ19÷30 የአምላካችን ቸርነትና የእመቤታችን ምልጃ አይለየን አሜን ፫ @Eftah_bemaleda 30 views09:06