2023-04-27 18:01:37
እንደሚታወቀው አንድ አውሮፕላን ከአንድ ቦታ ከመነሻው ተነስቶ ወደ ሌላ ቦታ ማለትም ወደ ግቡ መድረሻ ሲደርስ የሚያርፍበት የራሱ የሆነ ቦታ ወይንም ማረፍያ ሌላ ነገር የማይቀመጥበት ተደላድሎ የሚያርፍበት ቦታ እንዳለው የታወቀ ነው
ግን ደግሞ በረራ አድሮጎ ሲመጣ የሚያርፍበት ካጣና ካልተዘጋጀ ብሎም ስፍራው በተለያዩ ነገሮች ከሞላ ሊያርፍ ያሰበበትን ቦታ ይተውና ወደ ሌላ ስፍራ ጉዞውን ያደርጋል ለሱ ምቹውን ቦታ ስለሚፈልግ
"ክርስቶስም እንዲሁ ነው በእኛ ህይወት ሊሰራ ለእርሱ ምቹ የሆነውን የልባችን ቦታ ላይ ሊያርፍ ይፈልጋል ንፁህ የሆነ፣ ዝቅ የሚል፣ ትህትና የጨመታ፣ከንሰሃ ዝግጁ የሆነ "
ታዲያ እኛ ዛሬ ለእርሱ የሚሆን ቦታ ኖሮን ይሆን ልባችንስ ለክርስቶስ የሚሆን ምቹ ማረፊያ አድርገን አዘጋጅተንስ ይሆን በእኛ ሊሰራ ወዶና ፈቅዶ ሲመጣ ልባችን በሌሎች ነገሮች ተይዘው ቦታን አጥቶ እንዳያልፈንና ከመንገዱ እንዳንወጣ እንጠንቀቅ እንንቃም ዛሬ በልባችን ከተቀመጡ የክርስቶስን ቦታ ከወሰዱት ነገሮች ጌታ ያላቀን ንፁህ ልብንም ይፍጠርልን
"አቤቱ ንፁህ ልብን ፍጠርልኝ፣የቀናወን መንፈስህን በውስጤ አድስ" መዝ 51,10
ቦታ ባዘጋጀንለት ልክ ነውና ወደ እኛ የሚመጣው እናም ሲመጣ ሌሎች ነገሮችን "ጠጋ በሉ ብለን የማሸጋሸግ "እይሰራን ከእርሱ ጋር እኩል ቦታ ልንሰጠው ከሆነ ተሳስተናል
"ያዕቆብም ለቤተሰቡና ከእርሱ ጋር ላሉት ሁሉ እነዲህ አለ ፤እንግዶቹን አማልክት ከመሃከላችሁ አስወግዱ፥ ንፁሁንም ሁሉ ላብሳችሁን ለውጡ" ዘፍ 35,2
ከወንድማችሁ ቦና
@kekalumaed
111 viewsedited 15:01