Get Mystery Box with random crypto!

👏 ልባም ሴቶች 👏

የቴሌግራም ቻናል አርማ lebamsetoch — 👏 ልባም ሴቶች 👏
የቴሌግራም ቻናል አርማ lebamsetoch — 👏 ልባም ሴቶች 👏
የሰርጥ አድራሻ: @lebamsetoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 880

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-05-15 09:06:36 ተጋፈጪው!!



በብዙ ፈተናዎችና መከራዎች ማለፍ የማይቀር አስቀድሞ የሰው ልጅ በጥፋቱ ወደ ራሱ የሳበው ነው ታዲያ ዛሬ በመከራ በማለፋችሁ "ለምን " ብላችሁ ወደ እግዚያብሄር ዞራችሁ እንድታጉረመርሙ ሊያደርጋችሁ አይገባም ማንም ሰው ከአቅሙ በላይ የሆነ ሸክም የማያልፈውም ፈተና አልተሸከመምና ሰው እስከሆንን በፈተናና በብዙ የህይወት ገጠመኝ መከራ ማለፋችን የማይቀር ነው

ፈተናዎችሽን ተጋፈጪ አትሽሺያቸው የማይሸነፉ መከራዎች የሉምና ወዮ በቃ አበቃልኝ ፣ አቃተኝ ብለሽ ተስፋ እንዳትቆርጪ ዛሬ ላይ የከበቡሽ የህይወት ፈተናዎች ደፍረሽ ብትጋፈጪያቸው የማይሸነፉ ሆነው ነው ምን ጊዜም ማጉረምረምን በህይወትሽ ተቀዳሚ አታድርጊ ተስፋ መቁረጥንም አታንግሺ ልብ በይ

"ላያልፍ የመጣ ፈተና ላይሸነፍ የከበበሽ መከራ የለም "

ከችግሮችሽ አትሽሺ ተጋፈጪያቸው ደግሞም ታጋሽ ልብ ይኑርሽ እንዴት ቆይ ግን የእውነት መከራዎቼ ይሸነፋሉ ብጋፈጥ የምትይ አዎን ልብ በይ

ተጋፍጣ ፈተናዎቿን የምታሸንፍ ሴት የፀሎት ሴት የሆነች የእምነት ሴት የሆነች ናት ይህች ሴት የፀሎትና የእምነት ሴት ከሆነች እንዴት ተስፋ በመቁረጥ ህይወቷ ሊያበቃ ይችላል በፍፁም እንጂ የሚያበረታት ሃይልና አቅምን ብሎም እንዴት ማለፍ እንዳለባት "ጥበብን " የሚያጎናፅፋት እግዚያብሄር አለና

ምቹ ነገር ወይም በምቾት ህይወት ማለፍን ሁሌ አትጠብቂ ከምቾት ህይወት ወተሽ በመከራ አንድ እንደምታልፊ እወቂ የምትሰሪውም "ነገዋን አንቺ " የምታይውም በዚህ ውስጥ ነውና በፍፁም አታጉረምርሚ ልብ በይ "ላያልፍ የመጣ መከራ የለም" ስለዚህ ፅኚ የፀሎትና የእምነት ሴት ሁኚ ከእግዚያብሄር ጋር ያለሽ ህብረት ይጠንክር ያኔ ተጋፍጠሽ ማለፍ አይከብድሽም

አንቺ ሴት በርቺ ሁሉ ይታለፋልና ፅኚ

ከወንድማችሁ ቦና

ለአስተያየት @onlyforjesus1

Share @lebamsetoch
95 views06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 07:53:07 አንዳንድ ጊዜ



አንዳንድ ጊዜ ህይወት ሲከብደኝ ፣ ግራ ሲገባኝ ፣ የማደርገውን ሳጣ ሲጨላልምብኝም ነገሩ፣የምፈልገው ነገር በጊዜው ሳይመጣ ሳይሳካም ሲቀር

"በቃ ብሞትስ ! ከዚህ በላይ እንዴት ልታገስ አልቻልኩም በኑሮዬ ደስተኛ ካልሆንኩ ጌታ ቢወስደኝ አልያም እኔ ወደ እርሱ ብሄድ ምን አለበት " እያለኩ መሞቴን እየናፈቅኩ ለራሴ ብዙ አወራለው

በሚያልፈው መከራ እጅ ሰጥቼ በስንፍና ሃሳብ መሞቴን ብናፍቅም ግን ደግሞ አንዳንዴ ወደ ራሴ መልስ ስል ለምን እንደዚህ አልኩኝ ብዬ ራሴን ወቅሳለው እኔ ብዙ ህይወት ማሳለፍ ፈልጋለው እግዚያብሄር በእኔ ያሰበውን የልቡን ፈቃድ እስከመጨረሻው ፀንቼ ማድረግ ፈልጋለው እያልኩ ደግሞ በአንድ ጎን አብሰለስላለው ግን ደግሞ መከራን ጠልቶ ማማረር መፍትሄ አይሆን ነገር

እሺ አሁን በየትኛው ሃሳብ ልፅና እያልኩኝ ብዙ ካወረድኩና ካወጣው በኃላ እንዲህ ብዬ ልደመድም ወሰንኩ


"ለካ መሞቴን ጥቅም እንዲኖረው የሚያደርግልኝ መኖሬ ነው የመሞቴ ጥቅም ደግሞ በምኖረው ህይወት ላይ የተንጠለጠለ ነው መከራ አለ ብዬ ባማርር ውሰደኝ የሚል ጩኸትም እለት እለት ባስተጋባ ምኑ መሞቴን ጥቅሜ አደረገው በፈተና የሚፀና የተባረከ አይደል ለምን ፀንቼ አልቆምም መከራው ይበልጥ መሰሪያዬ እንጂ መጥፊያዬም አይደል ደግሞስ እጋፈጠውና አሸንፈውም ዘንድ ስልጣን ተሰጥቶኛል " ከሚል ውሳኔ ላይ ደረስኩ እላችኃለው

ስለዚህ 《መኖራችሁን ጠልታችው መሞታችሁን አትናፍቁ የእናንተ በህይወት መኖር ከእናንተ ይልቅ ብዙ የሚጠቅመው ሰው አለና!!》

ከወንድማችሁ ቦና

ለአስተያየት @onlyforjesus1

Share @lebamsetoch
35 views04:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 20:06:57 ደካማ ነኝ አትበይ!!



ደካማ ነኝ አትበይ
ደካማ አይደለሽም
ተስፋም አትቁረጪ
ይህ አይመጥንሽም
አልችልም አትበይ
ሁሉን ትችያለሽ
አንቺ በደም የተገኘሽ
አዲሷ ሄዋን ነሽ

ቦና

በፍፁም ስላለመቻል ለራስሽ አትውሪ ከቶውኑም ተስፋ ስለመቁረጥ ለአፍታ አታስቢ አዲሲቷ ሄዋን ተስፋ የማትቆርጥ እስከመጨረሻው ድረስ ልክ ለሆነው ነገር የምትሮጥ የምትፋለም እጇን ፈፅማ ለውድቀት የማትሰጥ ጉልበት እምነት ያለት ድንቅ ሴት ነትና

አልችልም ፣ አቃተኝ ሰለቸኝ አትበይ ችግሮችን ተጋፈጪ ከቶ አትሽሺያቸው እጅም እንዳትሰጪ መልካም ለሆነው ነገር ሁሉ እስመጨረሻው ሰዓት ድረስ ተጋደይ ያን የማድረግ አቅም አለሽና

ልብ በይ አለመቻልሽን ለራስሽ አታውሪ

ከወንድማችሁ ቦና

ለአስተያየት @onlyforjesus1

Share @lebamsetoch
134 views17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 20:26:15 ከ ገነት
174 views17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 15:28:45 ሰላም እንዴት ናችሁ

ይህን ነገር መናገር ፈልጋለው ለእህቶቼ ይጠቅማቸው እንደሆን የምትሉት ነገር ካለ ሃሳብ ማጋራት ይቻላል ብሎም ከራሴ ህይወት ገጠመኝና ካለፍኩት መከራ ቢማሩ የምትይው ካለም ይሀው ሰዓቱና ጊዜው ተመቻችቶልሻል ። ብቻ መናገር ፈልጋለው ውስጤ ሃሳብ አለ የምትሉም ይሀው ሰዓቱ

ለሃሳብ @onlyforjesus1

Share @lebamsetoch
186 views12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-04 09:53:35 በጊዜው!!



አዎን የፍቅር ግኑኙነት መጀመር ፣ አብሮ ከወደፊት አጣማሪ/አጋር ጋር ነው ከምንለው ሰው ጋር ሰፋ ያለ ጊዜ መውሰድ ብሎም መጨዋዋት ስለ ነገም ማሳብ እጅግ ደስ ያሰኛል መልካምም ነው ግን ይህ ሁሉ የሚያምረውና አግባብነት የሚኖረው ፍሬም የሚያፈራው ደግሞ በጊዜውና በእግዚያብሄር ፈቃድ መሰረቱን ካደረገ ብቻ ነው

እንዴት መልካምና ጣፋጭ ህይወት መሰላችሁ በእግዘሩ ፈቃድ ላይ ብሎም በጊዜው የፍቅር ግኑኙነት መጀመር

አታፍሩበትም
አትከስሩበትም

በችኮላ የራሳችሁንም ፈቃድ መነሻ አድርጋችሁ የገባችሁበት ግኑኙነት ነው እፍረትና ውርደት ያለበት ም/ቱም የራስን ፈቃድ ማራመድና ማስከተል የሚመራው ወደ ውድቀት ነውና አንቺ አንድን ወንድ ስለወደድሽው ብቻ አብረሽ የምትሆኚ ሴት ሆነሽ አትገኚ እውነት ነው አብሮ ለመሆን መውደድ አንዱ ግብዓት ነው ሆኖም ግን መውደድሽ ስሜታዊና በጊዜ የሆኑትን ነገሮች ያማከለ ከእግዚያብሄር ዘንድም ፈቃድን ካላገኘ ካልፀለይሽበት ለልብሽ መልስን ካልሰጠ ያ አደጋን ለህይወትሽ ያመጣል መውደድ ከስሜት በላይ ነውና

አዎን መረጋጋት ነው መፍትሄው "በችኮላና በደንታ ቢስነት የተመሰረተ ጎጆ በክረምት ዝናብ በበጋ ደግሞ ፀሃዩ እንደሚያገኘውና በጊዜ ሂደት ፈራሽ እንደሆነ ሁሉ ያለ ጊዜውና እግዚያብሄርንም ያላማከለ የፍቅር ግንኙነትም ልክ እንዲሁ ነው"

"ልባም ሴት አይኖቿ ወዳዩት ሁሉ እግሯ አይሮጡም"

ታያለች፣ ቆም ትላለች፣ ታስተውላለች፣ ከእግዜሩ ጋር ታወራለች ከዛም የሚበጀውን ውሳኔ ትወስናለች

ከወንድማችሁ ቦና

ለአስተያየት @onlyforjesus1

Share @lebamsetoch
123 viewsedited  06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 06:16:40 የውዶች ሁሉ ውድ ነሽ…



የወርቁ፣ የነሃሱና ብሩ አልፎም የከበሩት መዓድናት በሚመዘኑበት ሚዛን ላይ የሌለሽ ከእነርሱ ጋርም የማትስተካከዪ "የውዶች ሁሉ ውድ ነሽ"

ቅድስናን የተጫመትሽ፣ ክርስቶስን በልብሽ ያነገስሽ በሰው ዘንድ ተመን የማይወጣልሽ እንቁና የተለየሽ ውብ ልባም ሴት ነሽ

እንደ ዛፍ ቅጠል ቶሎ የልብሽ መልክ የማይጠወልግ ውብና ውድ ነሽ

አስተዋይ የሆንሽ ክርስቶስ የልቤ የሚልሽ አንቺዋ ልባም ሆይ ውድና ውድ ነሽ

ምነኛ ውድ ነሽ



አይንን ከሚስበው
ከብርና ከወርቅ
ብልጭልጭ ከሆነው
ከአልማዙ ይልቅ
እንቁ ይሁን ገንዘቡ
የማይጠጋጋሽ
አንቺ ልባም ሴት ሆይ
ምነኛ ውድ ነሽ

ቦና

" ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል። "
(መጽሐፈ ምሳሌ 31:10)

ለአስተያየት @onlyforjesus1

@lebamsetoch
416 views03:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 18:01:37 እንደሚታወቀው አንድ አውሮፕላን ከአንድ ቦታ ከመነሻው ተነስቶ ወደ ሌላ ቦታ ማለትም ወደ ግቡ መድረሻ ሲደርስ የሚያርፍበት የራሱ የሆነ ቦታ ወይንም ማረፍያ ሌላ ነገር የማይቀመጥበት ተደላድሎ የሚያርፍበት ቦታ እንዳለው የታወቀ ነው

ግን ደግሞ በረራ አድሮጎ ሲመጣ የሚያርፍበት ካጣና ካልተዘጋጀ ብሎም ስፍራው በተለያዩ ነገሮች ከሞላ ሊያርፍ ያሰበበትን ቦታ ይተውና ወደ ሌላ ስፍራ ጉዞውን ያደርጋል ለሱ ምቹውን ቦታ ስለሚፈልግ
"ክርስቶስም እንዲሁ ነው በእኛ ህይወት ሊሰራ ለእርሱ ምቹ የሆነውን የልባችን ቦታ ላይ ሊያርፍ ይፈልጋል ንፁህ የሆነ፣ ዝቅ የሚል፣ ትህትና የጨመታ፣ከንሰሃ ዝግጁ የሆነ "

ታዲያ እኛ ዛሬ ለእርሱ የሚሆን ቦታ ኖሮን ይሆን ልባችንስ ለክርስቶስ የሚሆን ምቹ ማረፊያ አድርገን አዘጋጅተንስ ይሆን በእኛ ሊሰራ ወዶና ፈቅዶ ሲመጣ ልባችን በሌሎች ነገሮች ተይዘው ቦታን አጥቶ እንዳያልፈንና ከመንገዱ እንዳንወጣ እንጠንቀቅ እንንቃም ዛሬ በልባችን ከተቀመጡ የክርስቶስን ቦታ ከወሰዱት ነገሮች ጌታ ያላቀን ንፁህ ልብንም ይፍጠርልን

"አቤቱ ንፁህ ልብን ፍጠርልኝ፣የቀናወን መንፈስህን በውስጤ አድስ" መዝ 51,10

ቦታ ባዘጋጀንለት ልክ ነውና ወደ እኛ የሚመጣው እናም ሲመጣ ሌሎች ነገሮችን "ጠጋ በሉ ብለን የማሸጋሸግ "እይሰራን ከእርሱ ጋር እኩል ቦታ ልንሰጠው ከሆነ ተሳስተናል


"ያዕቆብም ለቤተሰቡና ከእርሱ ጋር ላሉት ሁሉ እነዲህ አለ ፤እንግዶቹን አማልክት ከመሃከላችሁ አስወግዱ፥ ንፁሁንም ሁሉ ላብሳችሁን ለውጡ" ዘፍ 35,2

ከወንድማችሁ ቦና

@kekalumaed
111 viewsedited  15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 20:14:13 ፎቶ … ፎቶ… ፎቶ



ሰዎች በህይወት ሲኖሩ ብዙ ነገር ያስባሉ ጊዜ ፣ ሰዓትና ስፍራም ላሰቡት ሃሳብ መተግበሪያ ትልቅ ቁልፎች ሆነውም ይገኛሉ ያሰቡትን አንድ ሃሳብ ለመፈፀም ለሃሳቡ የሚመቸውን ነገር ከማድረግም አይቆጠቡም ስለዚህ ለሰው የሃሳቡ ጉዳይ የጊዜ የሰዓትና የስፍራ(ቦታ) ጉዳይም ጭምር ነው ማለት ነው ይህን ልል የወደድኩት ሰው ያለምክንያት አንድን ነገር ሊያደርግ አይችልም ብዙ ነገሩ የሃሳቡ ፅንስ ውጤት ነው

አንዲት ሴት ፎቶ ስትነሳ አስቀድማ አስባ ነው ለዚያም ነው የምታጌጠው ጊዜም ስፍራም የምትመርጠው ይህም ማለት ያቺ ሴት ዝግጅቷ አጠናቃ ነው የምትነሳው እንደማለት ነው ታዲያ ይህ ያቼን ሴት ሃጥያተኛ አልያም ክፉ አድራጊ አያደርጋትም ፍቶ መነሳት የተነሱትም ለሰዎች ማጋራት መልካም ነውና ታዲያ ግን የህይወት ጉዳዩ ከፎቶ ያለፈ ነው አብዝቶ እለት እለት ራስን ማሳየትና ጊዜም ማጥፋት ያ ግን አግባብ አይደለም

እኔ አንድ ሰው ፎቶ በተለያዩ መነናኛ ድህረ ገፆች ላይ ሲለቅ "አይ ጥሩ ይህ ሰው ማለት ይህ ነው ብዬ ፆታውን አልፎም ለሚያደርገው ነገር የምለው ካለኝ እንድለው ያደርገኛል ፎቶው ስለማንነቱ ፍንጭ ይሰጠኛልና ፎቶ የመልቀቁ ሚስጥርም ይህ ነው ሰው እንዲያውቀን " ታዲያ ግን እለት እለት ስፍራና ልብስ እየለዋወጠ አዝብዞ የሚለቅ ሰው እኔ ለዛ ሰው ያለኝን ግምት ዝቅ ያደርገዋል "የፎቶ ሰው " የሚል ቅፅል ስምም በኔ ዘንድ ይሰጠዋል

አስተውይ ስሚም አንቺ ሴት የምትኖሪለት አላማ ከፎቶ ያለፈ ነው ምክንያቱም የምትኖሪለት አላማሽ "ህይወት/ነፍስ" ነውና ጊዜሽን ማጥፋት ያለበት እዚህ ላይ ነው እለት እለት በራስሽ ፎቶ ማህበራዊ ድህረገፁን ከምታጨናንቂ ምናለ መልካም የሰውን ልብ የሚያፅናኑ ፁሃፎቶ፣ የሚያበረታቱ ቪድዬዎች፣ የመፅሃፍ ቅዱስ ጥቅሶችን መልቀቅ ብታበዢ ስንቱ ሰው ሰላምን ፍለጋ ምን ያህሉ ሰውስ ለጠመመች መንገዱ ምክርን ፍለገ ወደ እነዚያ ድህረ ገፆች እንደሚገባ አስተውለሽ ታውቂያለሽ በተለያዩ ልብሶች መዋብሽን የተለያዩ ስፍራዎች ላይ ተዘዋውረሽ ፎቶ መነሳሳትሽን መልቀቅሽን ሰው አይፈልገው ለዚያው በዚህ በመጨረሻው ዘመን ሰው ህይወትን ነው የሚሻው ከፎቶ ያለፈ ነገር ሰርተሽ እለፊ

"ባለ ፎቶዎ ሴት ተብለሽ በመጠራት ጊዜሽና ህይወትሽ አይባክን ባለ ፍቶዎ ከመባልም ያውጣሽ ንቂ ግብሽ ህይወት ነውና!!"

አስተውላ የሰማች ህይወት ታተርፋለሽ

ከወንድማችሁ ቦና

ለአስተያየት @onlyforjesus1

Share @lebamsetoch
75 views17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 08:53:36
125 views05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ