2022-07-08 11:02:50
የዐረፋ ቀን ዱዓ
ከዐብደላህ ብን ዐምር ብን አል’ዐስ እንደተወራው የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፦
وعن عبد الله بن عمرو بن العاص رضي الله عنهما أن النبي صلى الله عليه وسلم قال
((خَيْرُ الدُّعَاءِ دُعَاءُ يَوْمِ عَرَفَةَ ، وَخَيْرُ مَا قُلْتُ أَنَا وَالنَّبِيُّونَ مِنْ قَبْلِي : لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الْحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ))
رواه الترمذي ( 3585 ) وحسَّنه الألباني في " صحيح الترغيب " ( 1536 ) .
{ ከዱዓዎች ሁሉ በላጩ የዐረፋ እለት ዱዓእ ነው:: እኔም ሆንኩ ከኔ በስተፊት የነበሩ ነብያት ከተናገሩት መካከል በላጩ ቃል :- ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም ፣ እርሱም ብቸኛና አጋር የሌለው ነው ንግስናም ምስጋናም ለእረሱ ነው እርሱም በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው የሚለው ቃል ነው:: }
(ቲርሚዚይ (3585) ዘግበውታል ፤ ኢማሙ አልባኒ ሰሒሕ አት’ተርጊብ (1536) ላይ ሐዲሡን ሐሰን ብለውታል።)
የዚህ ዱዓ አጭር እና ጥቅል ማብራሪያ!
«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّه»ُ
“ላ ኢላሃ ኢለላህ” (ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም) ይህ የመጀመሪያው የዱዓ ክፍል “ከሊመቱ ተውሒድ” የተውሒድ ቃል በመባል ይታወቃል:: ይህ ቃል በሁለት መሰረታዊ ማእዘናት የቆመ ሲሆን:: ነፍይ {ማራቅ/ውድቅ ማድረግ} እና ኢሥባት {ማጽደቅ} ይባላሉ:: በዚህም ይህ የተውሒድ ቃል መጀመሪያው ነፍይ መጨረሻው ደግሞ ኢሥባት ይሆናል::
“ላ ኢላህ”(አምላክ የለም) የሚለው ቃል ሙሉ ለሙሉ ከአላህ ውጪ ከሚመለኩ አካላት በጠቅላላ አምልኮን ውድቅ ሲያደርግና ሲያርቅ::
“ኢለላህ” (ከአላህ በስተቀር) የሚለው ደግሞ የአምልኮ ተግባራትን በጠቅላላ ከነዓይነቶቻቸው ለአላህ ብቻ ያጸድቃል::
“ላ ኢላሃ ኢለላህ” ስንል ከአላህ በስተቀር ማንንም ምንንም አናመልክም ፣ ከአላህ በስተቀር ማንንም አንለምንም ፣ ከአላህ በስተቀር ለማንም አናርድም [በስሙ አንሰዋም {ለቀብርና ለጅን ለመሳሰሉት}] ፣ ከአላህ በስተቀር አምልኮን ለሌላ ለማንንም ቅንጣት ታክል አሳልፈን አንሰጥም እያልን ነው::
﴿قُلۡ إِنَّ صَلَاتِي وَنُسُكِي وَمَحۡيَايَ وَمَمَاتِي لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ﴾ [الأنعام: 162]
‘’ስግደቴ፣ መገዛቴም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ነው» በል፡፡’’ {አል አንዓም: 162 }
ይህ ነው ትክክለኛ የተውሒድ ቃል የሆነችው “ላ ኢላሃ ኢለላህ” ትርጓሜ:: ነፍይ እና ኢሥባት በማቆራኘት እንጂ አላህን በብቸኝነት ተመላኪ ማድረግ አይቻልም:: እነዚህ ሁለት ማዕዘናት “ላ ኢላሃ ኢለላህ” ጸንታ እንድትቆም የሚያደርጉ ናቸው::
« وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ »
“ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ” (ብቸኛና አጋር የሌለው ነው) የሚለው ሁለተኛው የዱዓው ክፍል ደግሞ የ “ላ ኢላሃ ኢለላህ”ን ትርጉምና ማዕዘናቱን የሚያጠናክር ነው::
“ወሕደሁ” (ብቸኛ ነው) የሚለው ኢሥባትን የሚያጠናክር ሲሆን ።
“ላ ሸሪከ ለሁ” (ተጋሪ የለውም) የሚለው ደግሞ ነፍይን ያጠናክራል::
በጥቅሉ ደግሞ “ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ” የሚለው “ላ ኢላሃ ኢለላህ” የምታመላክተውን ተውሒድ ያጠናክራል:: ተውሒድ ያለውን ታላቅ ደረጃና አንገብጋቢነትና ልዕቅናውን ያስገነዝባል::
«لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الْحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ»
“ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር”
(ንግስናም ምስጋናም ለእረሱ ነው እርሱም በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው።)
የሚለው የዱዓው ክፍል ደግሞ የተውሒድነ ማስረጃና መረጃዎቹን የሚጠቁም ነው::
አሸናፊና የበላይ የሆነው አላህ ከእርሱ ውጪ እውነተኛ አምላክ የለም ፣ ከእርሱ ውጪ በእውነት የሚመለክ እንደሌለ ያጠናክራል::
ንግስና ለእርሱ ነው ፣ በንግስናው ደግሞ ተጋሪ የለውም:: ምስጋናም በጠቅላላ ጥራት ለተገባው አላህ ነው:: ምክንያቱም አላህ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነውና:: በሰማይም ይሁን በምድር አንዳችም የሚያቅተው ነገር የለም::
በመሆኑም ይህችን ታላቅ ቃል እጅግ የላቀችና በላጭ የሆነች ቃል መሆኗን ልንረዳ ይገባል::
ይህን ጥያቄ ለጠየቀው ሰው አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው አላህ በመልካም ይመንዳው።
የዕውቀት ባለቤቶች እንደሚሉት የምናደርጋቸውን ዱዓዎችና ዚክሮች ይህም ይሁን ሌሎች በአግባቡ የሚጠቅሙንና በእኛ ላይም መልካም ተጽዕኖ ማሳደር የሚችሉት ትርጉማቸውን እየተገነዘብን የሚያመላክቷቸውን ቁም ነገሮች እየተረዳንና እያስተነተንን የምናደርጋቸው ሲሆን ነው::
ያለበለዚያ እንዲሁ በዘፈቀደ የምናነበንባቸው ከሆነ የምንለውን ሳናውቀውና ፣ የሚያመላክቱትን ቁም ነገር ሳንረዳ የምንል ከሆነ በእኛ ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ እጅግ አናሳና ደካማ ይሆናል::
ለዚህም ነው አብዛኛዎቹ ሰዎች ይህንን ዱዓ እያደረጉ፦
“ላ ኢላሃ ኢለላህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር”
ነገር ግን የሚሉትን በአግባቡ ስለማያውቁትና ስለማይገነዘቡት ይህንን ዱዓ አድርገው ብዙም ሳይቆዩ እጃቸውን አንስተው ከአላህ ውጪ ያለ አካል በማይችለው ነገር ላይ “እከሌ ሆይ! ድረስልኝ ከጭንቅ አውጣኝ” ሲሉ የሚደመጠው::
በአላህ እጠበቃለሁ! ከአላህ ውጪ ያለን አካል እጁን አንስቶ ከለመነ “ላ ኢላሃ ኢለላህ” ያለው የታል ??? የታለ ተውሒዱ???
﴿وَمَنۡ أَضَلُّ مِمَّن يَدۡعُواْ مِن دُونِ ٱللَّهِ مَن لَّا يَسۡتَجِيبُ لَهُۥٓ إِلَىٰ يَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ وَهُمۡ عَن دُعَآئِهِمۡ غَٰفِلُونَ﴾ [الأحقاف: 5]
“እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስም ለእርሱ የማይመልስለትን ከአላህ ሌላ ከሚጠራ ሰው ይበልጥ የተሳሳተ ማነው? እነርሱም ከጥሪያቸው ዘንጊዎች ናቸው፡፡”
{አል አህቃፍ :5 }
ስለዚህም ይህንንም ይሁን ሌሎች ዱዓዎችና ዚክሮችብ ስናደርግ ትርጉሙን በትክክል መገንዘብ ፣ የሚያመላክቱትን ቁም ነገር ማስተዋልና ማስተንተን አንገብጋቢ ጉዳይ ነው:: ይህን ማድረግ ስንችል በራሳችን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እና ላቅ ያለ ጥቅምን ማግኘት እንችላለን::
ምንጭ ፦ (ሸይኽ ዐብዱረዛቅ አል በድር (አላህ ይጠብቃቸው) “ፈዳኢሉ የውም ዐረፋ” በሚል ርዕስ በዙልሒጃ 8 / 12 / 1436 ባደረጉት ሙሐደራ ላይ ከትምህርቱ በኋላ ይህን ዱዓ እንዲያብራሩላቸው ከታዳሚ ለቀረበላቸው ጥያቄ ከሰጡት ምላሽ ለፅሁፍ በሚያመች መልኩ የተረጎምኩት ነው::)
{ሐይደር ኸድር}
[ሰኞ (የውሙ ዐረፋ)
ዙልሒጃ 9 / 12 / 1439
August 20 / 8 / 2018
ነሀሴ 14 /12 /2010]
https://t.me/SabahTube
۩••۩┈┈┈•⊰۩ ۩⊱•┈┈┈۩••۩
ጠቃማዊ መልዕክቶች እንዲደርስዎ…
Join Me
ሼር ማድረግ እንዳይረሱ!
Telegram:
https://t.me/haiderkhedir
YouTube:
52 views08:02