Get Mystery Box with random crypto!

Hello Ethiopia🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ helloethiopian — Hello Ethiopia🇪🇹 H
የቴሌግራም ቻናል አርማ helloethiopian — Hello Ethiopia🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @helloethiopian
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 877
የሰርጥ መግለጫ

ሰላም ለሁላችሁም በዚህ ቻናል የተለያዩ ዎቅታዊ እና እውነተኛ መረጃዎችን ታገኛላችሁ።
We are here to deliver updated News, Exclusive programs, Interviews, Entertainment and more Reliable and Updated Information about Ethiopia

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-02-09 17:28:13 የፌደራል መንግሥቱም ቢሆን ይህን ዐይን ያወጣ ጣልቃ ገብነት በገሀድ እያየ የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ምንም ዓይነት እርምጃ ባለመውሰዱ ዋነኛው ተጠያቂ ያደርገዋል፡፡


በሌላ በኩል የእምነቱ ተከታዮች የሃይማኖት ተቋማቸውን ትዕዛዝ በማክበር ጥቁር በመልበሳቸው ምክንያት በየመንገዱ እና በቤተ እምነታቸው ቅጥር ግቢ መደብደብ፣ ማዋከብ፣ ማሠር እና ማስፈራራት ደርሶባቸዋል፤ በተለይ በኦሮሚያና በአዲስ አበባ በሚገኙ መንግስታዊ የአገልግሎት መስጪያ ተቋማት ጭምር ተመሳሳይ በደል ሲደርስባቸው ተመልክተናል፡፡


ይኽ የዜጎችን ነፃነት መጋፋት ስለኾነ በምንም መንገድ ተቀባይነት የለውም። በኦሮሚያ ክልል የእምነቱ ተከታዮች ላይ እና የሃይማኖት አባቶች ላይ የሚደረጉ ማዋከቦች፣ እስሮች እና ግድያዎች አሁንም እየቀጠሉ በመሆኑ በአስቸኳይ ሊቆሙ ይገባል። ኢዜማ አሁንም የሃይማኖት ጉዳይ ውስጥ መንግሥት እጁን መክተቱ መዘዙ ከፍተኛ መሆኑን ደጋግሞ ማስገንዘብ ይፈልጋል፡፡


ድርጅታችን ኢዜማም ጉዳዩን በከፍተኛ ትኩረት እና በጥንቃቄ እየተከታተለ መሆኑን እያሳወቀ ለዚህ ሁሉ ውጥንቅጥ የዳረገን ብሔር ተኮር ፓለቲካ መሆኑን ለአፍታም ቢሆን አንዘነጋውም፤ የጥላቻ ፖለቲካን የፈለፈለው የብሔር አስተሳሰብ ሃይማኖት ውስጥም ገብቶ ሌላ ትርምስ ሲፈጥር ዝም ሊባል አይገባም እንላለን!

በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ያሉ ጽንፈኛ የብሔር ኃይሎች ህዝባችን ተረጋግቶ ለችግሮቹ በሰከነ መንገድ መፍትሔ እንዳያበጅለት ባገኙት የልዩነት ቀዳዳ ሁሉ የሚያደርጉትን ግፊት በቅጡ ማስተዋል እንደሚኖርብን ለማሳሰብ አንወዳለን፡፡


ኢዜማ እንደ አንድ ፖለቲካ ተቋም ችግሮቹ ተወሳስበው ወደ አላስፈላጊ መንገድ እንዳይሄዱና ተጨማሪ የሰው ሕይወት እንዳያስከፍለን ብሎም እንደሀገር ወደማንወጣው የማያባራ ውጥንቅጥ ውስጥ እንዳያስገባን እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ፓርቲ የምንችለውን ሁሉ ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማንል ለማሳወቅ እንወዳለን፡

ይህን መግለጫ ባወጣንበት ዛሬ እንኳን በወሊሶ መስመር በወለቴ፣ አለምገና እና ሰበታ ቀውሱ ተባብሶ ቀጥሏል፡፡

በተለያዩ ቦታዎች ሕይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የተሰማንን ጥልቅ ኀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን እንመኛለን፡፡


አሁንም በድጋሚ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጠረው ችግር በቤተክርስቲያኗ ቀኖና ከዚያም ካለፈ በሕግና በሕጋዊ መንገድ ብቻ እንዲፈታ እያሳሰብን፤ በአሁኑ ወቅት ግልፅ በሆነ መንገድ ጣልቃ እየገባ ያለው መንግሥት ለሀገር ሰላምና ደህንነት ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ተገንዝቦ ኃላፊነቱ ህግን አክብሮ ማስከበር መሆኑን በመረዳት እንዲንቀሳቀስ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡


የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

የካቲት 2/2015 ዓ.ም. ዓ.ም

https://t.me/helloethiopian
50 views14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 17:28:13 የጥላቻ ፖለቲካን የፈለፈለው የብሔር አስተሳሰብ ሃይማኖት ውስጥም ገብቶ ሌላ ትርምስ ሲፈጥር ዝም ሊባል አይገባም---ኢዜማ!


ኢዜማ በተቋሙ የተፈጠረውን ውስጣዊ ችግር ተከትሎ የመንግስት ኃላፊዎች ያደረጓቸው ንግግሮች ሁኔታውን ለተወሳሰበ ችግር ዳርገውታል ብሏል።


ሙሉ መግለጫው የሚከተለው ነው፡-


የጥላቻ ፖለቲካን የፈለፈለው የብሔር አስተሳሰብ ሃይማኖት ውስጥም ገብቶ ሌላ ትርምስ ሲፈጥር ዝም ሊባል አይገባም!


የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተፈጠረውን ችግር በአንክሮ እየተከታተለው ይገኛል፡፡

ጅማሬው ካሳደረበት ብርቱ ስጋት አንጻር ፓርቲያችን ጥር 23 ቀን 2015 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ ለማስገንዘብ እንደሞከረው የሃይማኖት ተቋማት ውስጥ የሚፈጠሩ ችግሮች መፈታት ያለባቸው በተቋሙ ህግና አሠራር መሠረት ሲሆን ይህን ውስጣዊ አሠራር አልፈው ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮች የሚኖሩም ከሆነ ያለምንም ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት በሕጋዊ መንገድ ብቻ ውሳኔ ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡


በዚህ ሂደት ውስጥ የመንግሥት ድርሻ መሆን የሚገባው በሕገመንግሥቱ አንቀጽ 11 ድንጋጌ መሠረት ፍጹም ገለልተኛነቱን በሚያረጋግጥ መልኩ በእኩልነት መርኅ ላይ ቆሞ ህግና ሥርዓትን ማስከብር ሲገባው በገሃድ ያሳየው ወገንተኝነት በእጅጉ አሳዝኖናል፤ ለተፈጠሩ ቀውሶችም ተጠያቂነት እንዳለበት ማስገንዘብ እንወዳለን።


በተቋሙ የተፈጠረውን ውስጣዊ ችግር ተከትሎ የመንግስት ኃላፊዎች ያደረጓቸው ንግግሮች ሁኔታውን ለተወሳሰበ ችግር ዳርገውታል።

ከመንግስት ሃላፊዎች አባባሽ ንግግሮች ባሻገር የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥትና የጸጥታ ኃይሉ በቤተክርስቲያኒቱ ውስጣዊ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት በተግባር ካሳዩት ወገንተኝነት እና አድሎ በከፋ መልኩ ባልታጠቁ እና ፈጽሞ የጸጥታ ስጋት ባልሆኑ ምእመናን ላይ ጭካኔ የተሞላበት የኃይል እርምጃ በመውሰዳቸው የንጹሐን ዜጎች ሕይወት እንዲቀጠፍ እና አካል እንዲጎድል ምክንያት ሆኗል፡፡


በክልሉ በተደጋጋሚ የሚስተዋሉ የንጹሐን ዜጎችን ሞት፣ አስከፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችና መፈናቀሎችን ተቆጣጥሮ ሰላምና ደኅንነትን ማስከበር ያልቻለው የክልሉ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ላይ ጣልቃ እየገባ እንደሀገር ያለንበትን ችግር ውስብስብ እያደረገው ይገኛል፡፡

የፌደራል መንግሥቱም ቢሆን ይህን ዐይን ያወጣ ጣልቃ ገብነት በገሀድ እያየ የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ምንም ዓይነት እርምጃ ባለመውሰዱ ዋነኛው ተጠያቂ ያደርገዋል፡፡


በሌላ በኩል የእምነቱ ተከታዮች የሃይማኖት ተቋማቸውን ትዕዛዝ በማክበር ጥቁር በመልበሳቸው ምክንያት በየመንገዱ እና በቤተ እምነታቸው ቅጥር ግቢ መደብደብ፣ ማዋከብ፣ ማሠር እና ማስፈራራት ደርሶባቸዋል፤ በተለይ በኦሮሚያና በአዲስ አበባ በሚገኙ መንግስታዊ የአገልግሎት መስጪያ ተቋማት ጭምር ተመሳሳይ በደል ሲደርስባቸው ተመልክተናል፡፡


ይኽ የዜጎችን ነፃነት መጋፋት ስለኾነ በምንም መንገድ ተቀባይነት የለውም። በኦሮሚያ ክልል የእምነቱ ተከታዮች ላይ እና የሃይማኖት አባቶች ላይ የሚደረጉ ማዋከቦች፣ እስሮች እና ግድያዎች አሁንም እየቀጠሉ በመሆኑ በአስቸኳይ ሊቆሙ ይገባል። ኢዜማ አሁንም የሃይማኖት ጉዳይ ውስጥ መንግሥት እጁን መክተቱ መዘዙ ከፍተኛ መሆኑን ደጋግሞ ማስገንዘብ ይፈልጋል፡፡


ድርጅታችን ኢዜማም ጉዳዩን በከፍተኛ ትኩረት እና በጥንቃቄ እየተከታተለ መሆኑን እያሳወቀ ለዚህ ሁሉ ውጥንቅጥ የዳረገን ብሔር ተኮር ፓለቲካ መሆኑን ለአፍታም ቢሆን አንዘነጋውም፤ የጥላቻ ፖለቲካን የፈለፈለው የብሔር አስተሳሰብ ሃይማኖት ውስጥም ገብቶ ሌላ ትርምስ ሲፈጥር ዝም ሊባል አይገባም እንላለን!

በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ያሉ ጽንፈኛ የብሔር ኃይሎች ህዝባችን ተረጋግቶ ለችግሮቹ በሰከነ መንገድ መፍትሔ እንዳያበጅለት ባገኙት የልዩነት ቀዳዳ ሁሉ የሚያደርጉትን ግፊት በቅጡ ማስተዋል እንደሚኖርብን ለማሳሰብ አንወዳለን፡፡


ኢዜማ እንደ አንድ ፖለቲካ ተቋም ችግሮቹ ተወሳስበው ወደ አላስፈላጊ መንገድ እንዳይሄዱና ተጨማሪ የሰው ሕይወት እንዳያስከፍለን ብሎም እንደሀገር ወደማንወጣው የማያባራ ውጥንቅጥ ውስጥ እንዳያስገባን እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ፓርቲ የምንችለውን ሁሉ ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማንል ለማሳወቅ እንወዳለን፡

ይህን መግለጫ ባወጣንበት ዛሬ እንኳን በወሊሶ መስመር በወለቴ፣ አለምገና እና ሰበታ ቀውሱ ተባብሶ ቀጥሏል፡፡

በተለያዩ ቦታዎች ሕይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የተሰማንን ጥልቅ ኀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን እንመኛለን፡፡


አሁንም በድጋሚ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጠረው ችግር በቤተክርስቲያኗ ቀኖና ከዚያም ካለፈ በሕግና በሕጋዊ መንገድ ብቻ እንዲፈታ እያሳሰብን፤ በአሁኑ ወቅት ግልፅ በሆነ መንገድ ጣልቃ እየገባ ያለው መንግሥት ለሀገር ሰላምና ደህንነት ስጋት እየፈጠረ መሆኑን ተገንዝቦ ኃላፊነቱ ህግን አክብሮ ማስከበር መሆኑን በመረዳት እንዲንቀሳቀስ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡


የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)

የካቲት 2/የጥላቻ ፖለቲካን የፈለፈለው የብሔር አስተሳሰብ ሃይማኖት ውስጥም ገብቶ ሌላ ትርምስ ሲፈጥር ዝም ሊባል አይገባም---ኢዜማ!


ኢዜማ በተቋሙ የተፈጠረውን ውስጣዊ ችግር ተከትሎ የመንግስት ኃላፊዎች ያደረጓቸው ንግግሮች ሁኔታውን ለተወሳሰበ ችግር ዳርገውታል ብሏል።


ሙሉ መግለጫው የሚከተለው ነው፡-


የጥላቻ ፖለቲካን የፈለፈለው የብሔር አስተሳሰብ ሃይማኖት ውስጥም ገብቶ ሌላ ትርምስ ሲፈጥር ዝም ሊባል አይገባም!


የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተፈጠረውን ችግር በአንክሮ እየተከታተለው ይገኛል፡፡

ጅማሬው ካሳደረበት ብርቱ ስጋት አንጻር ፓርቲያችን ጥር 23 ቀን 2015 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ ለማስገንዘብ እንደሞከረው የሃይማኖት ተቋማት ውስጥ የሚፈጠሩ ችግሮች መፈታት ያለባቸው በተቋሙ ህግና አሠራር መሠረት ሲሆን ይህን ውስጣዊ አሠራር አልፈው ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮች የሚኖሩም ከሆነ ያለምንም ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት በሕጋዊ መንገድ ብቻ ውሳኔ ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡


በዚህ ሂደት ውስጥ የመንግሥት ድርሻ መሆን የሚገባው በሕገመንግሥቱ አንቀጽ 11 ድንጋጌ መሠረት ፍጹም ገለልተኛነቱን በሚያረጋግጥ መልኩ በእኩልነት መርኅ ላይ ቆሞ ህግና ሥርዓትን ማስከብር ሲገባው በገሃድ ያሳየው ወገንተኝነት በእጅጉ አሳዝኖናል፤ ለተፈጠሩ ቀውሶችም ተጠያቂነት እንዳለበት ማስገንዘብ እንወዳለን።


በተቋሙ የተፈጠረውን ውስጣዊ ችግር ተከትሎ የመንግስት ኃላፊዎች ያደረጓቸው ንግግሮች ሁኔታውን ለተወሳሰበ ችግር ዳርገውታል።

ከመንግስት ሃላፊዎች አባባሽ ንግግሮች ባሻገር የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥትና የጸጥታ ኃይሉ በቤተክርስቲያኒቱ ውስጣዊ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት በተግባር ካሳዩት ወገንተኝነት እና አድሎ በከፋ መልኩ ባልታጠቁ እና ፈጽሞ የጸጥታ ስጋት ባልሆኑ ምእመናን ላይ ጭካኔ የተሞላበት የኃይል እርምጃ በመውሰዳቸው የንጹሐን ዜጎች ሕይወት እንዲቀጠፍ እና አካል እንዲጎድል ምክንያት ሆኗል፡፡


በክልሉ በተደጋጋሚ የሚስተዋሉ የንጹሐን ዜጎችን ሞት፣ አስከፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችና መፈናቀሎችን ተቆጣጥሮ ሰላምና ደኅንነትን ማስከበር ያልቻለው የክልሉ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ላይ ጣልቃ እየገባ እንደሀገር ያለንበትን ችግር ውስብስብ እያደረገው ይገኛል፡፡
48 views14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-09 13:42:23


67 views10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 08:45:39

73 views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 16:51:51
በመላው ዓለም የሚገኙ የኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ምዕመናን ጾመ ነነዌን ጥቁር ልብስ በመልበስ የጸሎት መርሐ ግብሮችን እየተካፈሉ ነዉ።
የኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም ባስተላለፈው ውሳኔ እና በሰጠው መግለጫ ከትናንት ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 3 ተከታታይ ቀናት በመላው ዓለም የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የሚገኙ ማናቸውም ካህናት እና ምዕመናን ሙሉ ጥቁር ልብስ በመልበስ በየ አብያተ ክርስቲያናት እና በገዳማት ያለውን ሥርዓተ ጸሎት እንዲመሩ እና እንዲከታተሉ ወስኖ ነበር።
ይህንን ውሳኔ ተከትሎ ምእመኑ ጾመ ነነዌን ጥቁር ልብስ መልበስ፣ በጸሎት መርሐ ግብሮች በመገኘት ጸሎት እያደረገ ይገኛል። ቅዱስ ሲኖዶሱ በሰጠው ውሳኔ መሰረት ከትናንት ጀምሮ ጠዋት ጠዋት ኪዳን እና ምሕላ፣ ቅዳሴ፣ የሰርክ የዐውደ ምሕረት መርሐ ግብር እንዲሁም ማታ ማታ የቤተሰብ ጸሎት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶሱ "ምእመናን ለጸሎት ወደ ቤተ ክርስቲያን በሚሄዱበት ጊዜ ለጸሎት ከሚያስፈልጉ መጽሐፍት ውጪ ሌላም ምንም ዓይነት መፈክር ይዞ መምጣት የማይቻል መሆኑን" አስታውቆ ነበር።
ፎቶዎቹ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን አዲስ አበባ ውስጥ በ ሲ ኤም ሲ ሚካኤል ፣ በቅድስት ሰዓሊተ ምህረት እና በቅዱስ እስቲፋኖስ አብያተ ክርስትያናት በፀሎት ሲሳተፉ የሚያሳዩ ናቸው። https://t.me/helloethiopian
85 views13:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 14:53:27
በጣሊያን የሥራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከፕሬዚዳንት ሰርጂዮ ማታሬላ ጋር መክረዋል።

ጣሊያን እና ኢትዮጵያ ለረዥም ጊዜ የቆየ እና ታሪካዊ የዲፕሎማሲ ግንኙነት የመሠረቱ ሀገራት መሆናቸው በምክክሩ ተጠቁሟል።

ሀገራቱ ያላቸውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ በሚያጠናክሩበት አግባብ ላይም መክረዋል።

የኢትዮጵያ እና የጣልያን ግንኙነት ለብዙ ዘመናት የቆየ እና ፍሬአማ የሆነ አጋርነት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስታውቀዋል። https://t.me/helloethiopian
110 views11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 12:17:03
ዛሬ በተጀመረው የህዝበ ውሳኔ ምርጫ ላይ በህግ ጥሰት የአንድ ምርጫ ጣቢያ ድምፅ አሰጣጥ ተቋርጧል::


ዛሬ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች የህዝበ ውሳኔ ድምፅ እየሰጡ ሲሆን በአንድ የምርጫ ጣቢያ ሂደቱ ተቋርጧል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንዳስታወቀው በወላይታ ዞን ስር በሌ የምርጫ ማዕከል ‘ሶርቶ’ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘው ሶርቶ 1 ምርጫ ጣቢያ ውስጥ የህግ ጥሰት መፈፀሙን አረጋግጫለሁ ብሏል።


በምርጫ ጣቢያው ድምፅ በመስጠት ሂደት ወቅት የቀበሌ አስተዳደር ሀላፊዎች በሶርቶ 1 ምርጫ ጣቢያ በመገኘት 105 የሚሆን የግለሰብ ጊዜያዊ መታወቂያዎችን ድምፅ ለመስጠት ለተሰለፋ ዜጎች በማደል ህገ ወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው ተገኝተዋል።


በዚህም የህግ ጥሰቱ እስከሚጣራ ድረስ ሶርቶ 1 ምርጫ ጣቢያ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን እንዲያቋርጥ መወሰኑ ታውቋል።
https://t.me/helloethiopian
113 views09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 11:46:01
በ2012 ዓመተ ምህረት በጸደቀው የመገናኛ ብዙሀን አዋጅ አንቀጽ 11 ላይ የሕዝብ ብሮድካስት አገልግሎት ስያሜ፣ በስምህ ተቋቁመው እ( ኢቢሲ ፣ አሚኮ ፣ ኢፕድ፣ ኢዜአ፣ ኦቢኤን፣ አዲስ ሚዲያ እና መሰሎቻቸው) የመክሰስ ሙሉ መብት አለህ። በአዋጅ አንቀጽ 11 ላይ፣ የሕዝብ ብሮድካስት አገልግሎት ባለፈቃድ የሀገሪቱን የቋንቋ፣ የባህል፣ የሃይማኖት፣ የፆታ፣ የፖለቲካ ብዝኃነትን የሚያንጸባርቁ እና የሕዝብን ጥቅም የሚመለከቱ ዓለም አቀፋዊ፣ ሀገራዊ፣ ክልላዊና አካባቢያዊ ጉዳዮችን ሽፋን የመስጠት ግዴታ እንዳለበት በግልጽ ይደነግጋል። https://t.me/helloethiopian
106 views08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ