Get Mystery Box with random crypto!

🇪🇹ዘወልድ ምክረ-ሕግ🇪🇹‼️

የቴሌግራም ቻናል አርማ khalidkebede — 🇪🇹ዘወልድ ምክረ-ሕግ🇪🇹‼️
የቴሌግራም ቻናል አርማ khalidkebede — 🇪🇹ዘወልድ ምክረ-ሕግ🇪🇹‼️
የሰርጥ አድራሻ: @khalidkebede
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.22K
የሰርጥ መግለጫ

ቻናሉ ሕጎችንና የፍ/ቤት ዉሳኔዎችን ያጋራል። አጫጭር የሕግ ማብራሪያዎችንና የምክር አገልግሎቶችን ይሰጣል።
ጠበቃ ካሊድ ከበደ እና ጠበቃ አማረ እሸቱ
በማንኛዉም የፌዴራል እና የክልል ፍ/ቤት ጠባቃና የሕግ አማካሪ
ስልክ- 0935439820
ኢሜይል- khalidbinkebe@gmail.com

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-11 20:50:18 የድርጅት ቦታ አይከፈልም የሚለውን መመሪያ ለፈለገ ሁሉ የአብክመ የተሻሻለዉ ስመ ንብረት ዝውውር መመሪያ
566 viewsKhalid Kebede, edited  17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-11 20:12:59 ስለ አስገድዶ መድፈር ወንጀል አንዳንድ ነጥቦች
******

ንጀል ሕጉ የስገድዶ መድፈ ወንጀልን ጨሮ ሌሎች በግረ ሥጋ ነፃነትና ንፅህና ላይ ስለሚፈፀሙ ወንጀሎች የተደነገገው ከአንቀጽ 620 ጀምሮ እስከ አንቀጽ 628 ባሉት ድንጋጌዎች ሲሆን የአንቀጽ 620 ንዑስ ቁጥር 1 ድንጋጌ “ማንም ሰው የኃይል ድርጊት በመጠቀም ወይም በብርቱ ዛቻ ወይም ሕሊናዋን እንድትስት ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ መከላከል እንዳትችል በማድረግ ከጋብቻ ውጪ አስገድዶ ከአንዲት ሴት ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት የፈፀመ እንደሆነ ከአምስት ዓመት እስከ አሥራ አምስት ዓመት በሚደርስ ፅኑ እሥራት ይቀጣል” ይላል፡፡
ከላይ በተጠቀሰው ድንጋጌ መሠረት የአስገድዶ መድፈር ተግባር ተፈፅሟል ለማለት፡-
1. ተጠቂዋ ሴት መሆን አለባት፣ (አንዲት ሴት ወንድን አስገድዳ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ከእርሷ ጋር እንዲፈፀም ያደረገች እንደሆነ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 621 መሠረት የምትጠየቅ ቢሆንም ሕጉ ይህን የወንጀል ድርጊት “አስገድዶ የመድፈር” (rape) በሚለው ሀረግ (ቃል) አይጠራውም፡፡
2. በማናቸውም መንገድ የሚደርስባትን ጥቃት መከላከል እንዳትችል የተደረገች መሆን አለባት፡፡ ማለትም በሴቷ ላይ ድርጊቱ የተፈፀመው ኃይልና ዛቻን በመጠቀም፣ ወይም ሕሊናዋን በማሳት እና በመሳሰለው መንገድ የመከላከል አቅሟን በማሳጣት ተደግፎ መሆን አለበት፡፡
3. የግብረ ሥጋ ግንኙነት መፈፀም አለበት (ወይም ቢያንስ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ለመፈፀም መሞከር ይኖርበታል)፣
4. ድርጊቱ የተፈፀመው የጋብቻ ግንኙነት በሌላቸው ሰዎች መካከል መሆን አለበት፡፡ በዚህም መሠረት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በጋብቻ ተሳስረው የሚገኙ ሰዎችን አይመለከትም ማለት ነው፡፡
1.9K viewsKhalid Kebede, edited  17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-11 19:56:15 በችልተኝነት ወንጀል ማድረግ ምን ማለት ነዉ? የሚያስከትለዉ ቅጣትስ?
****

ቸልተነት ከስሙ እደምንረዳው አድ ሰው ጥንቃቄ ማድረግ ሲገባው ሣያደርግ ሲቀር ነው፡፡ በዚህም የጥንቃቄ ጉድለት ምክንያት ያልተፈለገ እና ሊወገድ የሚችል ጉዳት ሲደርስ ነው፡፡ አንቀፅ 59(1) የቸልተኝነት አይነት ሁለት ናቸው፡፡
1. የታወቀ ቸልተኝነት
በ59 (1) (ሀ) መሠረት አንድ ሠው በታወቀ ቸልተኝነት ሊቀጣ የሚችለው ድርጊቱ በወንጀል የሚያስቀጣ ውጤት ሊያስከትል እንደሚቻል እያወቀ አይደርስም በሚል ግምት ወይም ባለማመዛዘን የፈፀመ እንደ ሆነ ነው፡፡ በሌላ አነጋግር ድርጊቱ ጉዳትን እንደሚያስከትል ያውቃል ሆኖም ግን የድርጊቱን ውጤት አይቀበልም፡፡ ምክንያቱም ድርጊቱ ጉዳት ያደርሣል ብሎ አያምንም ወይም ጉዳት ለመከላከል እያደረገ ያለው ጥንቃቄ በቂ በመሆኑ ጉዳት አይደርስም የሚል ግምት አለው፡፡
አንድ የታከሲ ሹፌር ባለቤቱ ስልክ ደውላ ስታናግረው የመኪናውን መፍጠን ተረድታ “ረጋ ብለህ ሂድ” ብላ ብትጠይቀውና እሱም፡፡ 15 አመት መኪና የመንዳት ልምድ አለኝ አታሰቢ ቢል” እና ከ2 ደቂቃ በኋላ ሰው ገጭቶ ቢገድል በዚህ አንቀፅ ይታያል
2. ያልታወቀ ቸልተኝነት
በአንቀፅ 59(1) (ለ) መሠረት ያልታወቀ ቸልተኝነት የሚባለው ወንጀል ፈፃሚው ድርጊቱ ጉዳት እንደሚያስከትል ሳያውቅ ሲቀር ወይም ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ባለመገንዘቡ ጉዳት ሲያደርስ ነው፡፡

****
ቸልተኝነትና እና ቅጣት:-
በአንቀፅ 59(2) መሠረት ቸልተኝነት በህጉ ላይ በተለይ ስቀጣል ተብሎ ካልተደነገገ በቀር በቸልተኝነት የተፈፀመ ወንጀል አያስቀጣም ስለሆነም አንድ ድርጊት ወይም ያለማድረግ በቸልተኝነት ቢፈፀሙ ሊያስቀጡ የሚችሉት ህጉ በግልፅ የወንጀል ተጠያቂነት መኖሩን ካስቀመጠ ነው፡፡
1.6K viewsKhalid Kebede, edited  16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-07 13:29:26 #እንድታውቁት

የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦዲት የቅሬታ ምንጭ ሆኖ የቆየው " የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 " ን በአዲስ መመሪያ እንዲተካ ማድረጉን አሳውቋል።

መመሪያውን ማሻሻል ያስፈለገበት ዋነኛ ምክንያት የታክስ አስተዳደሩን ቀልጣፋ ለማድረግ እና ግልጽነት የጎደላቸውን አሰራሮች ግልጽ ለማድረግ ነው ብሏል ሚኒስቴሩ።

አዲሱ መመሪያ ቁጥር 176/2014 በሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 ላይ የነበረውን አሰራር ያሻሽላል ተብሏል።

አዲሱ ወይም የተሻሻለው የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 176/2014 ከላይ በPDF ተያይዟል።

@tikvahethiopia
595 viewsKhalid Kebede, 10:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-05 21:35:41 የአስተዳደር መስሪያ ቤት ውል በግልግል ይታያል? አይታይም? የሚለው የህግ ነጥብ ላይ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተለያዬ አስገዳጅ የህግ ትርጉሞችን ሰጥቷል፡፡ ከነዚህም መካከል:-
1ኛ- በዘምዘም ፒኢልሲ እና በኢሊባቦር ዞን ትምህርት ጽ/ቤት መካከል ባለው ጉዳይ በሰ/መ/ቁ 16896 16/02/1998ዓ.ም በቅጽ 2 ገጽ 75-78 ላይ በተለይ ህግ ከከለከላቸው ነገሮች በስተቀር ተዋዋዮች የሚዋዋሉበትን ጉዳይ እንደመሰላቸው የመወሰን መብት እንዳላቸው የፍ/ህ/ቁ 1711 ስለሚገልጽ እና ውል ደግሞ ለተዋዋዮች ህግ ስለሆነ እንዲሁም ግራቀኙ በውላቸው ላይ አለመግባባቶች በግልግል እንደሚታዩ በግልጽ ስለተቀመጠ ውላቸው መከበር ስላለበት ጉዳዩ በቀጥታ በመደበኛ ፍርድ ቤት መታየት የለበትም
በማለት አስገዳጅ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ይህም ማለት ጉዳዩ በቅድሚያ በግልግል ዳኝነት መታየት አለበት የሚል ነው፡፡
2ኛ- በብሄራዊ የኢትዮጽያ ኢንሹራንስ ኩባንያ እና በዘላቂ ግብርና ተሀድሶ ኮሚሽን መካከል በፋ/መ/ቁ 27349 ታህሳስ 8/2000ዓ.ም ቅጽ 7 ላይ የተሰጠ ውሳኔ ሲሆን በይዘት ደረጃ የፍ/ህ/ቁ 1765(የዘመድ ዳኛ ስለመምረጥ) እና 1731 ድንጋጌን በመጥቀስ ጉዳዩ በውላቸው መሰረት የዘመድ ዳኛ በፍርድ ቤት በኩል አሰይሞ እልባት ማግኘት የሚገባው እንጅ በቀጥታ ለፍርድ ቤት መቅረብና ውሳኔ ሊሰጥበት የሚገባ አይደለም በማለትጉዳዩ በግልግል ዳኝነት መታየት እንደሚችል ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
3ኛ- በጣና ውሀ ጉድጓድ ቁፋሮ እና ድሬዳዋ አስተዳደር ውሀና ፍሳሽ ባለስልጣን መካከል በሰ/መ/ቁ 127459 መስከረም 23/2010ዓ.ም የተሰጠው ውሳኔ ከላይ ከየናቸው ሁለት ውሳኔዎች በይዘቱ ያፈነገጠ ነው፡፡ይዘቱም የፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 315(2) የአስተዳደር መስሪያ ቤት የግንባታ ውል ጉዳይ በግልግል ዳኝነት አይታይም በማለት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ይህ ውሳኔ
የመጀመሪያዎቹን ሁለት ውሳኔዎች በግልጽ አልሻራቸውም። በተግባር እንቅፋት ፈጥሯል፡፡ ሰበር ወጥ የሆነ የህግ ትርጉም ለመስጠት በሚል ቢቋቋምም የተቋቋመበትን አላማ ስቶ ህግ እየሰበረ ነው:: ተገማችና ወጥነት ያለው ውሳኔ ባለመስጠቱ ዳኞች የየራሳቸውን አቋም ለመያዝና የሰበርን ውሳኔዎች አስገዳጅነት ላለመቀበል ምክንያት ሆኗል! የተለየ ሀሳብ ካለ እስኪ ወዲህ በሉ ጓዶች! ሰላም አዳር!
858 viewsMengesha Eyasie, 18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-05 08:45:40 ኑዋሪነታቸው በሁለት የተለያዩ ክልሎች የሆኑ ሰዎች የገጠር መሬትን በተመለከተ የሚያደርጉት ክርክር መሬቱ በሚገኝበት ክልል ባለው የወረዳ ፍርድ ቤት የስረ ነገር ስልጣን ታይቶ ዕልባት ያገኛል:: ሰበር መዝገብ ቁጥር 106560 ያልታተመ!
612 viewsMengesha Eyasie, 05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-04 20:13:25 Non -arbitrable cases as per article 7 of proclamation 1237/2013
606 viewsMengesha Eyasie, 17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-02 10:59:49
አንድ ሰው በህግ አግባብ የመኖሪያ ቤት ለመስራት በማህበር የተደራጀ እና በስራ ምክንያት የተደራጀበትን አካባቢ መልቀቅ/የመኖሪያ አድራሻ መቀየሩ ከቤት ማህበር አባልነት አያሰርዝም።
862 viewsKhalid Kebede, 07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ