Get Mystery Box with random crypto!

ዘማሪ ክብሮም

የቴሌግራም ቻናል አርማ kebrom01 — ዘማሪ ክብሮም
የቴሌግራም ቻናል አርማ kebrom01 — ዘማሪ ክብሮም
የሰርጥ አድራሻ: @kebrom01
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 224

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-02-22 10:57:34 እዚያ ቦታ ላይ መገኘታቸው አባ መልአኩን ግራ አጋብቷቸዋል። እሳቸው ብቻ ሳይሆኑ በመንበረ ፓትሪያርኩ ጊቢ አብረዋቸው በአንድ ክፍል እንዲዳበሉ እና እንዲጠብቋቸው ትእዛዝ የተሰጣቸው አባ ገ/ሚካኤልም ግራ ተጋብተዋል።
ጥቂት ቀናት እንደተላመዱም እንዲህ ሲሉ ይጠይቋቸዋል።
"አባቴ ከየት ነው የመጡት!?" ይሏቸዋል አባ ገ/ሚካኤል።
"ከወላይታ ሶዶ።"
"ከእዚያ ምን ያደርጋሉ?"
"አስተምራለሁ።"
"ምን ያስተምራሉ?"
"መንፈሳዊ ትምህርት ነው፤ ወንጌል አስተምራለሁ።"
"ታዲያ አሁን ወደዚህ የመጡት ለምንድነው?"
"የመጣሁትማ ጠርተውኝ ነው።"
"ማነው የጠራዎት?"
"ቅድም ያመጡኝ ሰዎች ናቸው...ከእሳቸው ጋ ቆይ ያሉኝ።"
"ለምን ጉዳይ ነው የጠሩዎት?"
"አላውቅም።"
እኚህ አባት በትክክልም ለምን እንደተገኙ አያውቁም። እንዳውም እሳቸውን ያሳዘናቸው የብፁ አቡነ ቴዎፍሎስ በነበረው መንግስት መታሰር ነበር።
አባ መልአኩ ምክንያቱን በማያውቁት ጉዳይ ቆዩ መባላቸው ስልችት ብሏቸዋል። እና አንድ ቀን ጠባቂያቸው ወደጎረቤት ሄድ እንዳሉ እሳቸው ጊቢውን ጥለው ሄዱ።
ጠፉም ተባለ። የደርግ ደህንነቶች ፍለጋውን አጧጧፏት። ባህታዊው ቢጫ ሸማቸውን እንደተከናነቡ፣በባዶ እግራቸው፣ እግራቸው ወዳመራቸው ሲገሰግሱ ተያዙ።
እንግዲህ እኚህ መሾማቸውን ያላወቁ አባት ነበሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ ሆነው የተሾሙት፤ብፁዕ አቡነ ተክለሃይማኖት።
በተሾሙ ጊዜም ሹመቱን አልቀበልም፣ "መንበሩ ለእኔ አይገባም!" ብለው ነበር። አምርረውም አልቅሰዋል። እንዳይሰወሩም ጥበቃ ተሰማርቶባቸው ነበር።

አንድ ለመውጫ፥
የወቅቱ መንግስት ኮሚኒስት ነውና ብፁዕ አቡነ ተክለሃይማኖትን መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያንን አስመልክቶ ያናግሯቸዋል፥
"...አባታችን ይህንን ካቴድራል ወደ ሙዚየምነት ልንቀይረው እንፈልጋለን። ሌላ አለም ላይ እየተለመደ የመጣ ነው። ቤተ እምነቶች ወደ ሙዚየምነት እየተለወጡ ነው። እኛም አስበናል!" ይሏቸዋል።
እሳቸውም ድፍረታቸው እያስደነቃቸው፥
"ታዲያ ምን ችግር አለ። ትችላላችሁ! ...ግን ያንን ማድረግ የምትችሉት እኔን ገድላችሁ ነው!!" ብለዋል።
በነገራችን ላይ ብፁዕ አቡነ ተክለሃይማኖት አብዝተው የሚጾሙ እና የሚጸልዩ ነበሩ። ከእዚህ ምድር በድካም ሲያልፉም የሰውነት ክብደታቸው 25 ኪሎ ደርሶ ነበር።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዘመናቱ እንደተፈተነች ነው። የገዛ ልጆቿ፣ አገልጋዮቿ ሳይቀር እንደይሁዳ አሳልፈው ሰጥተዋት ያውቃሉ። ግን ሁሉንም አልፋ ዘመናትን ስትሻገር ነው የምትገኘው።
በረከታቸው ይደርብን።
መልካም የጾም፣የፀሎት ወራት ይሆንላችሁ ዘንድ ምኞቴ ነው።
ምንጭ፥ ከአቡነ ቴዎፍሎስ ግለ ታሪክ እና ሌሎች ታማኝ ድረ ገጾች።
(ውድነህ ክፍሌ)
34 views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 23:50:35
34 views20:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 23:50:29 አሐዱ ባንክ

ዓለም ፍትህ የላትም። ምድር ፍታሃዊነት አታውቅም።

ፍትህ ከራስህ ካልወጣ በስተቀር ከሌላው እጅ አትለምን።

አንተን የሚመስል ሌላውን ማይበድል ግዙፍ ተቋም እና ስርዓት ገንባ !!!
30 viewsedited  20:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 22:59:15
33 views19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 22:59:07 #መልካም_ዜና

ለቤተክርስቲያን ድምፅ በመሆን በኩረ ሰባክያን መምህር ምሕረተአብ አሰፋን ጨምሮ ፌቨን ዘሪሁንና በእርሱ የክስ መዝገብ ሥር የተካተቱት እህት ወንድሞቻችን እንዲሁም ጋዜጠኛ ዮሴፍ ተፈተዋል።

የቀሩትን ወንድሞችና እህቶችን ደግሞ እንዲሁ ተፈተው ለማየት ያብቃን።
34 views19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 22:59:38 https://vm.tiktok.com/ZMYBPcKRW/
41 views19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 15:18:25
51 views12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 15:18:18 ዘወረደ
የአቢይ ጾም የመጀመርያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል
ይህ ዕለት የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሳምንት ነው
አምላክ ከሰማይ ስለመውረዱ
ለሰው ልጆች በረከትን ስለማደሉ በስፋት ይነገራል
በዐቢይ ጾም ውስጥ ስምንት ሳምንታት ያሉ ሲሆን
ቅዱስ ያሬድ የየራሳቸው ስያሜ ሰይሟቸዋል
ዘወረደ
ቅድስት
ምኩራብ
መፃጉዕ
ደብረዘይት
ገብር ኄር
ኒቆዲሞስ
ሆሣዕና ናቸው
እነዚህ የየራሳቸው ምሥጢር እና ታሪክ ያላቸው ሲሆን
የመጀመሪያው ሣምንት ዘወረደ ይባላል
ከሰማየ ሰማያት የወረደው ከድንግል ማርያም የተወለደው
ለኩነተ ሥጋ የመጣው
ቅድመ ዓለም ከአብ ያለ እናት ድኅረ ዓለም
ከድንግል ማርያም ያለ እናት የተወደውን ልዩ ልደት ይነገራል

ይህ ጾም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ካሉት ሰባቱ አጽዋማት ታላቁና
ራሱ ጌታችን የጾመው ጾም ስለሆነ ልዩ ያደርገዋል።

ይህች የዘወረደ ሳምንት
ጾመ ሕርቃል በመባል ይታወቃል
ይህ ሳምንት በሕርቃል ስም የተሰየመው
የራሱ የሆነ ምሥጢር ያለው ሲሆን
በ714 ዓመተ ምህረት በቤዛንታይን ነግሦ የነበረ ንጉሥ ነው
በዘመኑ ፋርሶች ኢየሩሳሌምን ወረው የጌታችንን መስቀል ማርከው ወደ ፋርስ ወስደውት ስለነበረ ምዕመናን እያዘኑ ይኖሩ ነበረ

እባክህን መስቀሉን ከፋርስ ባባቢሎን አምጣልን አሉት
ንጉሡ ሕርቃል አማኝ ንጉሥ ስለነበረ
ከፋርሳውያን ጋር ከመዋጋቱ በፊቱ ሐዋርያት በሲኖዶስ
ነፍስ የገደለ ሰው እስከ ዕድሜ ልኩ ይጹም ብለው ሥርዓት
ሠርተዋልና ጾሙን ፈርቶ ስለነበረ
በኢየሩሳሌም የነበሩ የመስቀሉ ፍቅር ያደረባቸው ምዕመናን
በአንድነት ሆነው የአንድ ሰው ዕድሜ ሰባ ነው ቢበዛ ሰማንያ ነው
እኛ በኢየሩሳሌም የምንኖር ምዕመናን አንድ አንድ ሳምንት ስላንተ እንጾምልሃለን ብለውት ተስማምተው

ወደ ፋርስ ዘምቶ መስቀሉን ከፋርሳውያን እጅ ነጥቆ ይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሷል።

ይህንንም መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስያሜው ጾመ ሕርቃል ብላ ትጾመዋለች

ከዚህ በተጨማሪ ቅዱስ ያሬድ ስለ ዘወረደ
በስፋት በጾመ ድጓው ያመሰጥረዋል
ዘወረደ እምላእሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእምሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሀዩ በቃሉ
ከሰማይ የወረደውን ከድንግል የተወለደውን አይሁድ ሰቀሉት
የዓለም ጌታ መሆኑን አላወቁም
አይሁድ ከሰማይ የወረደው ከድንግል የተወለደው ማን እንደ ሆነ አላወቁም
በዚህ ዓለም ከባዱ ነገር
የእግዚአብሔርን አባታዊ ፍቅር አለመረዳት
እግዚአብሔር ከሰማይ ወደ ምድር የተጓዘውን ጉዞ አለማስተዋል
የተከፈልልንን ዋጋአለማቅ
ከባዱ ኃጢአት ይህ ነው

እግዚአብሔር የከፈለለትን ዋጋ የሚያውቅ ሰው
ክብሩን ሁሉ ለአምላኩ ሲል ይተዋል
አምላክ ከሰማይ ወርዷል ከድንግል ተወልዷል
እኔም አለኝ ከሜለው ሁሉ ልውረድ
ከአልጋ ወርጄ ፈቃደ እግዚአብሔርን ልፈጽም
ይላል
ግን በዚህ ዘመን ማን ይሆን እግዚአብሔር ደስ የሚሰኝበትን እየፈለገበረከትን የሚሻ
እባካችሁ
ማን እንደኛ የምትሉ
ጊዜው የኛ ነው የምትሉ
በዘር በፖለቲካ የምትወሸቁ
እባካችሁ ውረዱ
የቤተ ክርስቲያን አምላክ የወረደው እኛን ከፍ ሊያደርግ ነው
የተዋረደው እኛን ሊያከብረን ነው
የሞተው እኛን ሊያነሣን ነውና
እባካችሁ ወደ ልባችን እንመለስ

መዝሙሩም ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሃት ነው
ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ ይላል
መዝሙሩና የዕለቱ ስብከት እንመለስበታለን

የቅዱሳን አምላክ ማስተዋሉን ያድለን ጾሙን የበረከት ያድርግልን

ጸልዩ በእንተሰ ሰላም ስለ
ሰላም እንጸልይ
ስለ ሀገራችን እንጸልይ
ስለ ቤተ ክርስቲያን እንጸልይ
በጭንቅ በመከራስላሉት እንጸልይ
በልዩ ልዩ ጸዋትወ መከራ ስላሉት እንጸልይ
የሠራዊት አምላክ እግዚአብሔር ሰላሙን ያጽናልን

አባ አትናቴዎስ ወልደ ጎርጎርዮስ
አዲስ አበባ 11/06/2015
ሼር ማድረግዎን እንዳይረሱ
49 views12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 04:30:10
27 views01:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 04:30:07 [ብፁዕ አቡነ አብርሃም በዛሬው ዕለት ከተናገሩት የተወሰደ]

"ከሁለት ቀናት በፊት ሰላም መፈጠሩን ማወጃችን ይታወሳል። በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ የምንሰማቸው ነገሮች ሁሉ እንደገና ጆሮን ጭው የሚያደርጉ ቤተ ክርስቲያንን የሚከፋፍል አባቶችን ከልጆች ልጆችን ከአባቶች የሚያሻክሩ ነገሮችን እየሰማን ነው

"ወደ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ አዲሱ ሲኖዶስ በሚል አዲስ ስም እስካሁን ከሚጠቀሙበትም ለየት ባለ ስም የተሰጠ መግለጫ በሚል በሰጡት ባስተላለፉት ሁሉም በአንድነት ጵጵስናው የሚመለከታቸውም የማይመለከታቸውም የኤጲስ ቆጶስነቱ ደረጃም በስምምነቱም በጋራ የጠፋ ወይም የተሻረ የተደመሰሰ መሆኑን እያወቁም የቅድስናውን ልብስ በመልበስና ሌሎችም የስምምነቱ አካል ሆነው ስምምነቱን ያነበቡት ሳይቀሩ በአንድ ላይ ስምምነቱን ጥሰውታል ቀኖናውን እንደገና ደግመው ጥሰውታል። ሀይማኖቱንም ሕጉንም መልሰው መላልሰው ጥሰውታል።ሹመታቸው ሕጋዊ እንደሆነና በምንም ይሁን በምን የማይሻር መሆኑንም መልእክት አስተላልፈዋል። ይህ ከዕለት ወደ ዕለት የሚታይ የሚሰማ ከንቱ ክስ ሆኗል። ከሃይማኖታዊ ይልቅ ፖለቲካዊ ይዘትን ተጎናጽፏል። በሃይማኖታዊ መንገድ በሰላምና በፍቅር በክርስቶስ ደም የተመሠረተችውን ቤተ ክርስቲያን ከመጠበቅ በክርስቶስ ደም የተዋጁትን ምእመናን ከማስተማር ይልቅ በኃይልና በጉልበት ሁሉንም በነገረ ሰሪነት ግጭት በመፍጠር ሁሉንም ለመቆጣጠር ከዕለት ወደ ዕለት ደፋ ቀና ሲሉ ይታያሉ"

"አስተሳሰባቸው አነጋገራቸው ሁሉ በእኩል ደረጃ እንደሆኑም ተናግረዋል። 25 የተባሉትም የትናንትና ካህናት አገልጋዮች አሁንም ኤጲስ ቆጶሳት እንደሆኑ ተደርጎ ተንጸባርቋል። ዘጠኝ ሰዓት ላይ ይህንን አድርገው ቀኑን ሙሉ አንመጣም ሲሉ ዉለው 10 ሰዓት ላይ ግን ለማንም ለማን መጣን ሳይሉ ቤታቸው ውስጥ[ቤተ ክህነት] ገብተዋል። ... ቤተ ክርስቲያንም እስቲ ሁሉንም ነገር በትዕግሥት እንየው በማለት ዝም ብለን እየተመለከትን ነው። ስለዚህ ሕግን የጣሰ ሰው ስምምነትን ያፈረሰ ሰው ዛሬም ደግመው ደጋግመው እውነት ለማስመሰል ሐሰትን በሚለፍፉ ሰዎች እንዲህ ዓይነት ድፍረት የሚመለከተው አካል ሊመለከተውና አሁንም በቃ ሊለው ይገባል ብለን መልእክታችንን እናስተላልፋለን።"

ተዋሕዶ ሚድያ
25 views01:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ