Get Mystery Box with random crypto!

ለጸሎት ተነሱ 9/12 /2014 ማታ 4 ሰዓት የሚጸለይ ጸሎት ውዳሴ | "ቃለ እግዚአብሔር "

ለጸሎት ተነሱ

9/12 /2014 ማታ 4 ሰዓት የሚጸለይ ጸሎት
ውዳሴ ማርያም የለቱ
መዝሙረ ዳዊት 98እስከ113
ገላቲያ ምዕራፍ 5
እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ12
በእንተ ማርያም መሀረነ ክርስቶ12
የግል ጥያቄያችንን ጠይቀን አመስግነን
በአባታችንሆይ ጸሎት እንዘጋለን
መልካም የጸሎት ጊዜ አምላክ ጸሎታችንን ይቀበል
ልመናችንን ይስማ
ለጸሎት ተነሱ
""ጾምህና ምጽዋትህ ሁለት ዋጋ አላቸው፡፡ ከሰው ክብርን ሽተህ የምትጦም ከሆነ ኃጢአት በአንተ ላይ እንድትበረታ ደንቁርናህም እጅግ ጽኑ እንዲሆን እወቅ፡፡ ነገር ግን እጆችህን ለተቸገረ ሰው የምትዘረጋ ሕሊናህን ግን ወደ አምላክ ከሆነ፣ እንዲሁም ስትጦም ጦምህን በእግዚአብሔር ፊት ያደረግህ እንደሆነ ከፈጣሪህ የምታነሣዘንድ መልካምን ዋጋ ትቀበላለህ፡፡ ይህ ኃይለ ቃል “ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና፡፡”(ማቴ.6፡21) ብሎ ጌታችን ካስተማረው ትምህርት ጋር አንድ ዓይነት ትርጉም ያለው ነው፡፡
ጦምና ምጽዋታችን በከንቱ ፈቃዳችን ምክንያት ለኃጢአት አሳልፎ እንዳይሰጠንና በደላችንንም እጥፍ ድርብ እንዳያደርግብን አምላካችን ይህን ማስተዋል ዘወትር ይሰጠን ዘንድ በዚህ የጦም ወር እንለምነው፡፡ ለወደደንና በእኛ ጥቂት ድካም ዘለዓለማዊ ዋጋን ለሚሰጠን ለእርሱ ምስጋና ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

(ቅዱስ ኤፍሬም)