Get Mystery Box with random crypto!

ELAFE TUBE

የቴሌግራም ቻናል አርማ jezaeeislamwi — ELAFE TUBE E
የቴሌግራም ቻናል አርማ jezaeeislamwi — ELAFE TUBE
የሰርጥ አድራሻ: @jezaeeislamwi
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.78K
የሰርጥ መግለጫ

"በጊዜያቱ እምላለሁ ፤ ሰው ሁሉ በእርግጥ በኪሳራ ውስጥ ነው ፤ እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት ፥ በእውነትም አደራ የተባባሉት ፥ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ"
ሱረቱል ዐስር፦(1፥3)
ያሎትን ቅሬታ ሀሳብ አስተያየት በዚህ bot ይንገሩን
➱ @Foziblz_bot
Owner
➱ @yomiffyyy

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-06 21:45:48 የነገውን የሀሙስ ፃም እንዳያመልጠን እንፁመው። ብዙ መልካም ነገሮችን አቅፎ የያዘ ነው።

①) ነብዩ ሲፃሙት የነበረ የውዱ ነብያችን ሱና ነው
②) ስራዎች ወደ አላህ የሚወጣበት ቀንም ጭምር ነውና ስራችን ፃመኛ ሆነን አላህ ዘንድ እንዲቀርብልን የሚያደርግ ነው።
③) ይህ ቀን ደግሞ እጅግ ውድ በሆኑት የዙልሂጃ አስር ቀናቶች ውስጥ መገኘቱ ሌላው መለያ ነው።
④) በዙልሂጃ የሚፃም ሱና ፃም ከሌላ ጊዜ ከሚፃመው የበለጠና የላቀ አጅር ስለሚያስገኝ
⑤) ከነገ ወዳ እለተ ጅሙአ የአረፋ ፃም ነው። ነብያችን ጅሙአን ብቻ ነጥሎ መፃምን ከልክለዋል። ጅሙአን መነጠልን ሳይሆን አረፋ ፃም በጅሙአ ቀን ስለተከሰተ መፃሙ የሚቻል ቢሆንም አንዳንድ ኡለማዎች ለጥንቃቄ ሀሙስንም ብንጨምር ብለዋልና ይህም ሌላ መለያ ነው።
381 views ⚘يارب خفف ه‍مي ووجعي فاُنت وهحدك تحلم بحالي وم يجري بنفسي وك يو, 18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 11:15:51 የኡድሒያን እርድ የሚመለከቱ ጥቂት ወሳኝ ነጥቦች
-
ኡድሒያ ማለት በዒደል አድሓ ቀን ወደ አላህ ለመቃረብ ታስቦ የሚታረድ እርድ ነው፡፡ ነብዩ ﷺ በተግባር ፈፅመውታል፡፡ መዲና ላይ አስር አመት ሲኖሩም ኡድሒያን ያርዱ ነበር፡፡ (ሚሽካት፡ 1475) እንዲፈፀምም አዘዋል፡፡ ስለዚህ አቅም ያለው ሰው ሊፈፅመው ይገባል ማለት ነው፡፡ ነብዩ ﷺ “አቅሙ እያለው ኡድሒያን ያላረደ ሰው መስገጃችንን እንዳይቀርብ” ብለዋል፡፡ (ከኡድሒያ ጋር የተያያዙ እጅግ አስፈላጊ ነገሮች፡-
የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት አለበት :-

1. የሚታረደው እንስሳ ከሚከተሉት የእንስሳት አይነቶች ብቻ መሆን አለበት፡- በግ፣ ፍየል፣ ከብትና ግመል፡፡
2. ከነዚህ እንስሳቶች የትኛውን ማረድ ነው የሚበልጠው? በቅደም ተከተል ግመል፣ ከብት፣ በግ፣ ፍየል፣ ግመል በጋራ፣ ከብት በጋራ።
(ፈትዋ ለጅነተ ዳኢማህ) (ኢብኑ ዑሠይሚን፡ አሕካሙል ኡድሒያ ወዘካት)
* ከብትና ግመልን በጋራ ማረድ የፈለገ አንዱ ለ7 ሰው ነው መሆን አለበት፡፡
* ፍየልና በግ ለጋራ ማራድ አይቻልም፡፡

3. የሚታረደው እንስሳ እድሜው የደረሰ መሆን አለበት፡፡ በግ 6 ወር፣ ፍየል 1 አመት፣ ከብት 2 አመት፣ ግመል ከሆነ 5 አመት የሞላው መሆን አለበት፡፡

4. የሚታረደው እንስሳ እውር፤ በሽተኛ፤ አንካሳ፤ በጣም ያረጀ፣ አብዛኛው ወይም ግማሽና ከዚያ በላይ የሆነ ጆሮው፣ ጅራቱ፣ ላቱ፣ ቀንዱ፣ የተቆረጠ ወይም የተሰበረ መሆን የለበትም፡፡

5. የሚታረደው እንስሳ ህጋዊ በሆነ መልኩ የራስ ንብረት መሆን አለበት፡፡ (የተሰረቀ፣ የተነጠቀ፣ የተጭበረበረ ..መሆን የለበትም።)

6. የሚታረደው የግድ በተገደበው ጊዜ መሆን አለበት፡፡ እሱም ከዒድ ሶላት በኋላ እስከ ዙልሒጃ 13 ባሉት አራት ቀናት ውስጥ ነው፡፡ ነብዩ ﷺ (ዒድ) ከመሰገዱ በፊት ያረደ በሷ ቦታ (እርዱን) ይድገም፡፡ ያላረደ ይረድ” ይላሉ፡፡ (ቡኻሪ)

7. ያለምንም ልዩነት ከሁለቱም ፆታ ከወንድም ከሴትም ለኡድሒያ ማረድ ይፈቀዳል፡፡ (ኢብኑ ባዝ፣ ፈታዋ ኑሪን ዐለደርብ፡ ካሴት ቁ. 72)

8. ቆዳውንም ይሁን የትኛውንም ክፍሉን መሸጥ አይፈቀድም፡፡ ለአራጁ የሚከፈለውም ከኡድሒያው ቆዳ ወይም ሌላ ክፍሉ መሆን የለበትም፡፡ ነብዩ ﷺ “የኡድሒያውን ቆዳ የሸጠ ኡድሒያ የለውም” ብለዋል፡፡ (ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 2/1055) ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- “ከኡድሒያው ስጋ፣ ሞራ፣ ቆዳ፣ ወይም ሌላ ነገር መሸረጥ ክልክል ነው፡፡ ምክኒያቱም ለአላህ ያወጣው ገንዘብ ስለሆነ ልክ እንደ ሰደቃ መመለስ አይቻልም፡፡ (ፈታዋ ኢብኒ ዑሠይሚን፡ 25/162) ባይሆን ስጦታ የተሰጠው ሰው ቢሸጥ ምንም ችግር የለበትም፡፡

9. ስጋው ምን ይደረጋል? በእለቱ ከቤት ይበላል፤ ለዘመድ፣ ለጓደኛ፣ ለምስኪን ይሰድቃል ወይም ስጦታ ይሰጣል፣ ቀሪ ከኖረ ያስቀምጣል፡፡ ስጦታ የተሰጠው ሰው ግን መሸጥን ጨምሮ ሐላል በሆነ መልኩ ለፈለገው አገልግሎት ማዋል ይችላል፡፡

10. ኡድሒያውን እራሱ ባለቤቱ ቢያርድ በላጭ ነው፡፡ ካልቻለ ወይም ካልተመቸው ግን ሰው መወከል ይችላል፡፡
ከተለያዩ ፈትዋዎች የተሰበሰበ ነው፡፡
429 views ⚘يارب خفف ه‍مي ووجعي فاُنت وهحدك تحلم بحالي وم يجري بنفسي وك يو, 08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 07:13:54 ጨዋና ጥብቅ የሆንሽው ውድ እህቴ ሆይ! እስቲ የተወሰኑ ነገሮችን ልምከርሽ ጆሮ ስጪኝ፡፡ ከጆሮሽ በፊት ወደ ቀልብሽ እንዲደርስ የምፈልገው መልዕክት አለኝ፡፡
:
እህቴ … በሸሪዓው የማይኖሩ፤ አላህ (ሱብሃኑታአላ) ያዘዛቸውን የማይሰሙና የማይቀበሉ ሴቶች በዝተዋልና መብዛታቸውን አይተሽ አትታለዪ፡፡ በሒጃብ ጉዳይ ችላ የሚሉ ሴቶች በርክተዋልና ከነርሱ አትሁኚ፡፡ ወንድ ጓደኛ የሚይዙ፣ በፍቅር ሥም አላስፈላጊና ሐራም ግንኙነት የመሰረቱትን አይተሽ አትሞኚ፡፡ ዓላማቸውና ወሬያቸው ሁሉ ፊልምና ቲያትር ብቻ በሆኑት እህቶች አትሳቢ፡፡
:
ይበልጥ በግልጽ እንምከርሽ … በርግጥ ፈተናዎች በዝተዋል፣ መከራዎች በግራ በቀኝ አይለዋል፡፡ እይታን የሚፈትኑ፣ መስሚያን የሚፈትኑ፣ …አንዳንዶቹ ዝሙት ምንም አይመስላቸውም፣ ሌሎች የገንዘባቸው ምንጭ ምንነት የማያሳስባቸውም፡፡ ተቆጣጣሪ እንደሌለው ሆነው እንደፈለጉትና እንደሻቸው ይኖራሉ፡፡
:
ይህ ዘመን በርግጥ ነቢዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያሉት ዘመን ሳይሆን አይቀርም፡፡ ምን አሉ መሰለሽ … ‹ከኋላችሁ ትዕግስትን የሚጠይቅ ዘመን አለ፡፡ በዚያን ዘመን ውስጥ መታገስ ፍምን እንደመጨበጥ ነው፡፡ የናንተን ዓይነት ተመሳሳይ የሆነ መልካም ሥራ የሚሰራ ሰው የሃምሳ ሰው ምንዳ ያገኛል፡፡ …› ሐዲሡን ቲርሚዚ፣ አልሓኪምና ሌሎችም ዘግበውታል፡፡
:
አዎን … በመጨረሻው ዘመን የመልካም ሰሪ ሰው ምንዳው ብዙ ነው፡፡ ለምን ከተባለ በመልካም መንገድ ላይ ብዙ አጋዦች አይኖሩትምና ነው፡፡ በአመጸኞች መካከል የሚኖር ባይተዋር ብቻ ሆናል፡፡ አዎን ብቸኛ… እነርሱ ሙዚቃ ያዳመጣሉ እሷ አታዳምጥም፣ ሐራም ነገር ያያሉ እሷ አታይም፣ ቦይ ፍሬንድ ይይዛሉ እሷ አትይዝም … ሌላው ቀርቶ በድግምት እና በሺርክ ጭምር ውስጥ ይገባሉ፤ እሷ ግን ከሁሉም የራቀች ነፃ ናት፡፡
:
ሙስሊም በዘገቡት ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ‹ እስልምና ባይተዋር ሆኖ ተጀመረ ባይተዋር እንግዳ ሆኖ ይመጣል፡፡ ባይተዋር ሆኑት ምንኛ ታደሉ!.. › ብለዋል፡፡ አዎን ዕድለኞች ናቸው፡፡ እነዚያ ወንጀሎች በበዙበት ዘመን ጽድቅ የሚሰሩ፣ ሰዎች ሲያጠፉ የሚያስተካክሉ፣ ሌሎች ሲያምጹ የሚታዘዙ …
:
በቡኻሪ ዘገባ ደግሞ የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ‹ጌታችሁን እስከምትገናኙበት ቀን ድረስ አንድ ቀን መጥቶ ሌላ አይተካም ክፋቱ የባሰ ቀን የተተካ ቢሆን እንጂ፡፡› ብለዋል፡፡
:
አልበዛር በዘገቡት ሐዲሥ ደግሞ ሀያሉና ተከበረው አላህ ‹በሀያልነቴ እምላለሁ በባሪያዬ ላይ ሁለት ጊዜ ስጋትን አላደርግበትም፡፡ ሁለት ደህንነትንም አላደርግለትም፡፡ በምድር ላይ እያለ ከኔ ያልተጠነቀቀ እንደሆነ በመጨረሻው ዓለም ስጋት ውስጥ ነው፡፡ በምድር ላይ እያለ እኔን ከፈራና ከተጠነቀቀ ደግሞ የትንሳኤ ቀን ደህንነትን እሰጠዋለሁ፡፡› ብሏል፡፡
:
አዎን … በምድር ላይ እያለ አላህን ሲፈራና ሲያልቀው የኖረ ሰው የትንሳኤ ቀን የደህንነት ዋስትና አለው፡፡ ስጋትም ሆነ ፍራቻ የለበትም፡፡ ከአላህ ጋር በመገናኘቱ ይደሰታል፡፡ ጀነት በገባ ጊዜ እንዲህ በማለት ከባልደረቦቹ ጋር ይጠያየቃል፡፡ አላህ (ሱብሃኑታአላ)
:
‹የሚጠያየቁ ሆነውም ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይዞራል፡፡ ‹እኛ ፊት ቤተሰቦቻችን ውስጥ (የአላህን ቅጣት) ፈሪዎች ነበርን፡፡ አላህም በኛ ላይ ለገሰ፡፡ የመርዛም ቅጣት እሳት ቅጣትንም ጠበቀን፡፡ እኛ ከዚህ በፊት እንለምነው ነበር፡፡ እነሆ እርሱ በጎ ዋይ አዛኝ ነውና፡፡›ይላሉ፡፡›› (አጥ-ጡር ፡ 25-28) ካላቸውም መካከል ይሆናል፡፡
:
የወንጀል ባለቤት የሆነና በአላህ ሲያምጽ የኖረ፣ ሙሉ ሀሳቡንና ትኩረቱን ሆድና ወሲብ ላይ ያደረገ፣ የአላህን ቅጣት ያልፈራ፣ ለማስጠንቀቂያው ቁብ ያልሰጠ ሰው ደግሞ … በመጨረሻው ዓለም በፍራቻ ውስጥ ይኖራል፤ ድንጋጤም ይወርሰዋል፡፡

تَرَى الظَّالِمِينَ مُشْفِقِينَ مِمَّا كَسَبُوا وَهُوَ وَاقِعٌ بِهِم
‹በዳዮች ከሰሩት ሥራ የፈሩ ሆነው ታያቸዋለህ፡፡ እርሱም በነርሱ ላይ ወዳቂ ነው …› (አሽ-ሹራ ፡ 22)
:
ውድ እህቴ… ግልጽ በሆነው እውነት ላይ ነሽና በጌታሽ አላህ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እውነተኛ መመካትን ተመኪ፡፡ በዲን ላይ ጽኑዎች ትንግርት ቢሆኑም ከነርሱ ለመሆን ጣሪ፡፡ አጥፊዎች የተበራከቱ ቢሆንም ብዛታቸውን አይተሽ አትታለዪ፡፡
:
አላህ በጥበቃው ይጠብቅሽ፡፡ በእዝነቱ ያካብብሽ፡፡ እሱን ከሚፈሩ አማኞችም ያድርግሽ፡፡ ወደሱ ጎዳና መንገድ ከሚጣሩትና ያወቁትን ከሚተገብሩትም ያድርግሽ፡፡
:
ውድ እህታችን … ምክራችንን የማትቀበዪ ብትሆኚ እንኳን ሁሌም እህታችን ነሽ፡፡ መልካም ነገር እንመኝልሻለን፡፡ በሌሊትም ሆነ በቀን አላህን ዱዓእ እናደርግልሻለን፡፡ ዘወትር አንችን ከመምከርና ከመጠበቅ ወደኋላ አንልም፡፡ ጥረታችን ውጤት እንደሚኖረው በአላህ ላይ ተስፋ አለን፡፡ ስኬት ከርሱ ዘንድ ነው፡፡
:
የአላህ ሰላም እዝነትና በረከት በናንተ ላይ ይሁን፡፡
431 views ⚘يارب خفف ه‍مي ووجعي فاُنت وهحدك تحلم بحالي وم يجري بنفسي وك يو, 04:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 19:28:04 በዓረፋ ቀን ልንተገብራቸው የሚገቡ ዋና ዋና ተግባራት የትኞቹ ናቸው?

ኢብኑ ረጀብ ለጣኢፉ አል-መዓሪፍ በተባለው ኪታባቸው ላይ የጠቀሱትን እና ሌሎችም ዑለማዎች ከጠቆሟቸው ነጥቦች ከዋና ዋናዎቹ የተወሰኑትን በአጭሩ እንመልከት:‐
ኢብኑ ረጀብ እንዲህ ይላሉ:- “በዓረፋ እለት ከእሳት ነፃ መውጣቱን እና ለወንጀሎቹ ምህረትን የሚፈልግ ሰው ለዚያ ሰበብ የሚሆኑ ነገሮችን መፈፀም ይኖርበታል:: ከነዚያ ሰበቦች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል:-
የዓረፋን ቀን መፆም:-
አቡ–ቀታዳ ረዲየላሁ ዓንሁ እንዳስተላለፉት:‐«የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ስለ እለተ ዓረፋ ጾም ተጠየቁ፤ እሳቸውም "ያለፈውን እና የመጪውን አመት ሀጢአት ያስምራል ብዬ በአላህ ላይ ተስፋ አደርጋለሁ" አሉ።» (ሙስሊም ዘግበውታል)

መላ አካላትን አላህ ከከለከላቸው ነገሮች ማራቅ በተለይ ፈፅሞ አላህ ምህረት ከማያድርግለት ወንጀል በእሱ ላይ ማጋራት (ሺርክ) እራሱን መጠበቅ ይኖርበታል::

የተውሂድ መገለጫ የሆነውን እና የአላህን አጋር የሌለው ብቸኛ አምላክነት እንዲሁም በሁሉ ነገር ላይ ቻይነት የሚያረጋግጠውን “ላ ኢላሃ ኢለላሁ ወህደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሀምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢ ቀዲር ” የሚለውን ዚክር ማብዛት:: ይህ ዚክር በእለቱ አላህን ከምናወድስባቸው ቃላት የተሻለውና ምርጡ እንደሆነ መልእክተኛው ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ስለ ዓረፋ ቀን ዱዓእ በተናገሩበት ወቅት እንዲህ ሲሉ አሳውቀዋል:– "እኔና ከኔ በፊት የመጡት ነብያት ከተናገርነው ንግግር ሁሉ በላጩ ይህ ነው።"

አላህን ምህረት እንዲያደርግለት እና ከእሳት ነፃ ከሚወጡት ባሮቹ እንዲያደርገው አብዝቶ መለመን:: የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:- “ከዓረፋ ቀን የበለጠ አላህ ባሮቹን ከእሳት ነፃ የሚያወጣበት ቀን የለም::” (ሙስሊም ዘግበውታል)
በተጨማሪም ዱዓእ ተቀባይነት ሊያገኝበት ከሚችልባቸው ቀናት መካከል አንዱ እና ልዩ ቀን ነው:: መልእክተኛው ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ በማለት የዓረፋ ቀን ዱዓእ ገልፀዋል:- “ከዱዓኦች ሁሉ በላጩ የዓረፋ ቀን የሚደረግ ዱዓእ ነው::” ስለሆነም በዚህ ቀን ለራሳችን፣ ለወላጆቻችን፣ ለልጆቻችን፣ ለባለቤቶቻችን፣ ለቅርብ ዘመዶቻችን፣ በኛ ላይ ሀቅ ላላቸው እና ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ ሁሉ በርትተን ዱዓእ ልናደርግ ይገባል።

በአጠቃላይ በተሰማራንበት ቦታ ሁሉ በቻልነው አቅም መልካም ነገሮችን ከማድረግ እንዲሁም አላህን ከማውሳት ልንሳነፍ አይገባም:: በተለይ ከሰላት በኋላ ተክቢራ ማድረግ ከዛሬው እለት ፈጅር ሰላት የሚጀምር መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም:: ይህም ማለት ተክቢራ ማድረጉ ዛሬ የተጀመረው ከአምስቱ ግዴታ ሰላቶች በኋላ የተገደበ (ሙቀየድ) በመባል የሚታወቀው ነው እንጂ ከዚያ ውጪ ያልተገደበ (ሙጥለቅ) በመባል የሚታወቀው የተክቢራ አይነት እስከ አያመ-አተሽሪቅ ማብቂያ ማለትም የአስራ ሶስተኛው ቀን ፀሀይ እስከትጠልቅ ድረስ ይቀጥላል::

አላህ በመልካም ስራ ላይ ያበረታን እንዲሁም ይቀበለን!

https://t.me/hidayatv
435 views ⚘يارب خفف ه‍مي ووجعي فاُنت وهحدك تحلم بحالي وم يجري بنفسي وك يو, 16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 09:44:12 ☞ #የሴት ፈተና ኢስላምክን እንዲህ ሊያስጥልክ
ይችላልና ተጠንቀቅ **
ﺍﻟﻨﺴﺎﺀ ﻣﻦ ﺍﻋﻈﻢ ﺍﻷﺳﺒﺎﺏ ﺍﻟﺘﻲ ﺗﻨﻘﺺ ﺍﻳﻤﺎﻥ ﺍﻟﺮﺟﻞ
በሚስር(ግብፅ) ከተማ ውስጥ መስጂድን በአዛን
በሰላት አጥብቆ የሚይዝ አንድ ሰው (ሙዓዚን) ነበር። በርሱም ላይ ጥሩ መታዘዝ እና የኢባዳህ ብርሃኖች ይታዩበት ነበር፡፡

ከእለታት አንድ ቀን አዛን ሊያደርግ ወደ መናራህ
ወጣ፡ ታዲያ አዛን ላይ ሆኖ ከመስጂዱ ስር ወዳሉ ነስራኒዮች ቤት አይኑን ሲልክ ድንገት ከአንዱ ቤት ውስጥ አንዲትን እንስት ይመለከታል ከመቅፅበት
በውበቷ ተመርኮ ፈተና ላይ ይወድቃል ፡

በፍጥነትም እርሷ ወዳለችበት ቤት ይሄድና ዘው ብሎ ይገባል ልጅቱም ምን ፈልጎ እንደመጣ ትጠይቀዋለች
#እርሱም፡- እንዲህ ሲል መለሰላት አንቺን ነው
የምፈልገው
#እርሷም ፡- ለምንድን ነው እኔን የፈለከኝ?"
ብላ ጠየቀችው
#እርሱም፡- ልቤ ባንቺ ተፈትኗል የልቤን
መሰባሰቢያ ይዘሺዋል አላት
#እርሷም፡- ያለምንም ጥርጥር መቼም እሺ
ልልህ አልችም አለቸው
#እርሱም፡- እንግዲያውስ አገባሻለሁ" አላት
#እርሷም ፡- አንተ ሙስሊም ነህ እኔ ነስራኒይያህ
(ክርስቲያን) ነኝ አባቴ ደግሞ እንዲህ ሆነህ አንተን አይድረኝም አለችው"
#እርሱም፡- "ግዴለም እኔ ላንቺ ስል ነሳራ (ክርስቲያን) እሆናለሁ አላት፡
#እርሷም ፡-እንደዛ ያደረግክ እነደሆን (ክርስቲያን ከሆንክ) እኔም ፍቃደኛ ነኝ (አገባሀለሁ)
ከዚያም ይሄ ሰው እርሷን ለማግባት ሲል ነሳራ
(ክርስቲያን) ሆነና ከነርሱ ጋር ቤት ተቀመጠ
ታዲያ በዚያኑ እርሷን ጠይቆ ባገባበት የሰርጉ
ዕለት ቤቱ ውስጥ ወዳለ ከፍ ወዳለ ቆጥ ሲወጣ ወደቆ ወዲያኑ # ህይወቱ_አለፈች ፡:
እርሷንም ሳያገኝ እስልምናውን አጥቶ በኩፍር
ላይ ሞተ ። (አል፡ዳኡ ወ’ደዋአ ሊኢብኑ አል፡ቀይም ገፅ 167)

ሰዓይድ ኢብኑ ሙሰየብ(አላህ ይዘንለትና) እንዲህ
ይል ነበር፡ <<አላህ ሱብሀነ ወተዓላ አንድንም ነብይ አላከም፡ሸይጣን በሴት ፈተና ሲያጠፋቸው ከነርሱ ላይ ተስፋ ባይቆርጥ እንጂ>>
(መውሱዓቱ ኢብኑ አቢ ዱንያ ቅጽ 4 ገፅ 540)
አል-ሀሰን ኢብኑ ሳሊህ(አላህ ይዘንለትና) እንዲህ
ሲል ይናገራል፡ <<ሸይጣን ለሴት ልጅ እንዲህ ሲል ሰምቻለሁ፡አንቺ የኔ ግማሽ ጎኔ ነሽ፡እኔ በአንቺ
የምወረውርብሽ ቀስቴ ነሽ ደግሞም ባንቺ
ከወረወርኩ አልስተም፡እንቺ የሚስጥሬ ቦታ ነሽ፡አንቺ የኔ የጉዳዬ መልክተኛ ነሽ>>
(መውሱዓቱ ኢቡኑ አቢ ዱንያ ቅፅ 4 ገፅ 539)

ለወንድ ልጅ ከባዱ ፈተና የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ አለሂ ወሰለም እንድህ ብለዋል ለወንዶች ከሴቶች ይበልጥ ጎጂ ፈተና በኋላዬ አልተውኩም
(ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል)


--------------------
mohammed ebnu seid
-----------------------------

በቴሌግራም ይ ላ ሉን!


@Lewetatoch_mekir

https://t.me/Ethio_Suna_Media

https://t.me/Ethio_Suna_Media
399 viewsAbu Umar Ibnu Sadik, 06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 05:25:00 የመጀመሪያዉ መሰረት ጌታን ማወቅ ነዉ
''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''''

فَإِذَا قِيلَ لَكَ: مَا الأُصُولُ الثَّلاثَةُ التِي يَجِبُ عَلَى الإِنْسَانِ مَعْرِفَتُهَا؟
ላንተ፡ “በሁሉም ሰው ላይ ማወቁ ግዴታ የሚሆኑት ሶስቱ መሰረቶች የትኞቹ ናቸው?” ብትባል

فَقُلْ: مَعْرِفَةُ الْعَبْدِ رَبَّهُ، وَدِينَهُ، وَنَبِيَّهُ مُحَمَّدًا صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ.

“ባሪያ ጌታውን፣ ሃይማኖቱን እና ነብዩ ሙሐመድን - አላህ ሶላትና ሰላሙን በሳቸው ላይ ያውርድና - ማወቁ ነው” በል፡፡ [ ]

ኪታቧ “አልኡሱሉ አሥሠላሣህ” የሚለው ስሟን ያገኘችው ከነዚህ ሶስት መሰረቶች ነው፡፡ በግልፅ እንደሚታየው እነዚህ ሶስት መሰረቶች በቁርኣንና በሐዲሥ መሰረት ያላቸው እውነታዎች ናቸው፡፡ ይህም ከመሆኑ ጋር አንዳንድ በሙታን አምልኮ ፍቅር የተለከፉ ሰዎች ኪታቧን “ኡሱሉ አሽሸይጧን” “ስላሴ” ወዘተ እያሉ ሲያብጠለጥሉ ይሰማሉ፡፡ ይሄ ምን ያክል ከስነ-ምግባር የራቁ ዋልጌዎች እንደሆኑ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ “አልኡሱሉ አሥሠላሣህ” ወይም “ሶስቱ መሰረቶች” እያንዳንዱን ሰው የሚጠብቁ የቀብር ጥያቄዎች ናቸው፡፡ የሚከተለው ሐዲሥ ይህን ይህን ይጠቁማል፡፡ ከበራእ ኢብኑ ዓዚብ - አላህ ይውደድላቸውና - ተይዞ እንዲህ ይላሉ፡- “ከአላህ መልእክተኛ - አላህ ሶላትና ሰላሙን በሳቸው ላይ ያውርድና - ጋር ሆነን ከአንሷር ሰዎች የሆነን ጀናዛ ይዘን ወጣን፡፡ መቃብር ስንደርስ ገና ለሕዱ አልተዘጋጀም፡፡ (ለሕድ ማለት ቀብር ከተቆፈረ በኋላ ወደ ቂብላ አቅጣጫ ከስር አግድም ተቆፍሮ አስከሬኑ የሚገባበት ጓዳ ነው፡፡) የአላህ መልእክተኛ - አላህ ሶላትና ሰላሙን በሳቸው ላይ ያውርድና - ተቀመጡ፡፡ ልክ ከእራሳችን ላይ ወፎች ያረፉብን እስከሚመስል ተረጋግተን በዙሪያቸው ተቀመጥን፡፡ በእጃቸው እንጨት ይዘው መሬቱን ይመታሉ፡፡ እራሳቸውን ቀና አደረጉና ሁለት ጊዜ ወይም ሶስት ጊዜ {ከቀብር ቅጣት በአላህ ተጠበቁ} አሉ፡፡” በሌላ ዘገባ ደግሞ እንዲህ ብለዋል፡- {(ቀባሪዎች) ሲመለሱ የጫማቸውን ኮቴ ይሰማል፡፡ ያኔ ለሱ ‘አንተን ነው! ጌታህ ማነው? ሃይማኖትህ ምንድን ነው? ነብይህ ማነው?’ ይባላል}ብለዋል፡፡ በሌላ ዘገባ ደግሞ እንዲህ ብለዋል፡- {ሁለት መልአኮች ይመጡና ያስቀምጡታል፡፡ ‘ጌታህ ማነው?’ ሲሉት ‘ጌታዬ አላህ ነው’ ይላል፡፡ ‘ሃይማኖትህ ምንድን ነው?’ ሲሉት ‘ሃይማኖቴ ኢስላም ነው’ ይላል፡፡ ‘ይሄ ወደናንተ የተላከው ሰው ምንድን ነው?’ ሲሉት ‘እሱ የአላህ መልእክተኛ ነው’ ይላል፡፡ ‘(እንደሆነ) ምን አሳወቀህ? ሲሉት የአላህን መፅሐፍ አንብቤ አመንኩኝ፣ እውነት አልኩኝ ይላል፡፡’} በሌላ ዘገባ ደግሞ {አላህ እነዚያን ያመኑትን በቅርቢቱም ህይወት በመጨረሻይቱም (በመቃብር ውስጥ) በተረጋገጠው ቃል ያፀናቸዋል የሚለው ይህንን ነው፡፡ ከሰማይ የሆነ ተጣሪ፡ ‘ባሪያዬ እውነት ብሏል፡፡ ስለሆነም ከጀነት አንጥፉለት፡፡ ከጀነትም አልብሱት፡፡ የጀነትንም በር ክፈቱለት’ ሲል ይጣራል፡፡ መአዛውም ሽቶውም ይመጣለታል፡፡ በቀብሩም ውስጥ አይኑ የሚደርስበትን ያክል ይሰፋለታል፡፡ ካፊሩ ደግሞ… ሩሑ ወደ አካሉ ትመለሳለች፡፡ ሁለቱ መልአኮች ይመጡና ያስቀምጡታል፡፡ ከዚያም ‘ጌታህ ማነው?’ ሲሉት ‘ሃህ ሃህ አላውቅም’ ይላል፡፡ ‘ሃይማኖትህ ምንድን ነው?’ ሲሉት ‘ሃህ ሃህ አላውቅም’ ይላል፡፡ ‘ይሄ ወደናንተ የተላከው ሰው ምንድን ነው?’ ሲሉት ‘ሃህ ሃህ አላውቅም’ ይላል፡፡ ‘አስተባብሏል፡፡ ከእሳት አንጥፉለት፡፡ ከእሳትም አልብሱት፡፡ ወደእሳት የሚያደርስም በር ክፈቱለት’ ሲል ከሰማይ ተጣሪ ይጣራል፡፡ ከዚያም ከሙቀቷም ከመርዟም ይመጣበታል፡፡ የጎን አጥንቶቹ እስከሚተላለፉ ድረስ ቀብሩ ይጠበብበታል፡፡ ከዚያም እውርና ዲዳ የሆነ የብረት መንዶ የያዘ (የጀሀነም ጓድ) ይመደብበታል፡፡ (መንዶው) ተራራ ቢመታበት አፈር ያደርገዋል፡፡ በዚያም ሰውና ጂን ሲቀር ከምስራቅ እስከምዕራብ ያለው ሁሉ የሚሰማው ምት ይመታዋል፡፡ ከዚያም አፈር ይሆናል፡፡ ከዚያም ሩሑ ትመለሳለች፡፡... }ብለዋል፡፡ [አልባኒ “ሶሒሕ” ብለውታል፡፡ ሶሒሕ አትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 3558]
549 views ⚘يارب خفف ه‍مي ووجعي فاُنت وهحدك تحلم بحالي وم يجري بنفسي وك يو, 02:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 21:32:23 وَاللَّهُ جَعَلَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا وَجَعَلَ لَكُم مِّنْ أَزْوَاجِكُم بَنِينَ وَحَفَدَةً وَرَزَقَكُم مِّنَ الطَّيِّبَاتِ ۚ أَفَبِالْبَاطِلِ يُؤْمِنُونَ وَبِنِعْمَتِ اللَّهِ هُمْ يَكْفُرُونَ

አላህም ከነፍሶቻችሁ (ከጎሶቻችሁ) ለእናንተ ሚስቶችን አደረገ፡፡ ለእናንተም ከሚስቶቻችሁ ወንዶች ልጆችን፣ የልጅ ልጆችንም አደረገላችሁ፡፡ ከመልካሞችም ጸጋዎች ሰጣችሁ፡፡ ታድያ በውሸት (በጣኦት) ያምናሉን በአላህም ጸጋ እነሱ ይክዳሉን

وَيَعْبُدُونَ مِن دُونِ اللَّهِ مَا لَا يَمْلِكُ لَهُمْ رِزْقًا مِّنَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ شَيْئًا وَلَا يَسْتَطِيعُونَ

ከአላህም ሌላ ከሰማያትም ከምድርም ምንንም ሲሳይ የማይሰጧቸውን (ምንንም) የማይችሉትንም ይግገዛሉ፡፡

فَلَا تَضْرِبُوا لِلَّهِ الْأَمْثَالَ ۚ إِنَّ اللَّهَ يَعْلَمُ وَأَنتُمْ لَا تَعْلَمُونَ

ለአላህም አምሳያዎችን አታድርጉ፡፡ አላህ (መሳይ እንደሌለው) ያውቃል፡፡ እናንተ ግን አታውቁም፡፡

۞ ضَرَبَ اللَّهُ مَثَلًا عَبْدًا مَّمْلُوكًا لَّا يَقْدِرُ عَلَىٰ شَيْءٍ وَمَن رَّزَقْنَاهُ مِنَّا رِزْقًا حَسَنًا فَهُوَ يُنفِقُ مِنْهُ سِرًّا وَجَهْرًا ۖ هَلْ يَسْتَوُونَ ۚ الْحَمْدُ لِلَّهِ ۚ بَلْ أَكْثَرُهُمْ لَا يَعْلَمُونَ

በምንም ላይ የማይችለውን በይዞታ ያለውን ባሪያና ከእኛ መልካም ሲሳይን የሰጠነውን እርሱም ከእርሱ (ከሰጠነው) በምስጢርና በግልጽ የሚለግሰውን (ነጻ) ሰው አላህ (ለጣዖትና ለርሱ) ምሳሌ አደረገ፡፡ (ሁለቱ) ይተካከላሉን ምስጋና ለአላህ ይኹን፡፡ በእውነቱ አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡

وَضَرَبَ اللَّهُ مَثَلًا رَّجُلَيْنِ أَحَدُهُمَا أَبْكَمُ لَا يَقْدِرُ عَلَىٰ شَيْءٍ وَهُوَ كَلٌّ عَلَىٰ مَوْلَاهُ أَيْنَمَا يُوَجِّههُّ لَا يَأْتِ بِخَيْرٍ ۖ هَلْ يَسْتَوِي هُوَ وَمَن يَأْمُرُ بِالْعَدْلِ ۙ وَهُوَ عَلَىٰ صِرَاطٍ مُّسْتَقِيمٍ

አላህም ሁለትን ወንዶች (ለከሓዲና ለምእመን) ምሳሌ አደረገ፡፡ አንደኛቸው በምንም ነገር ላይ የማይችል ዲዳ ነው፡፡ እርሱም በጌታው ላይ ሸክም ነው፡፡ ወደ የትም ቢያዞረው በደግ ነገር አይመጣም፡፡ እርሱና ያ እርሱ በቀጥተናው መንገድ ላይ ኾኖ በማስተካከል የሚያዘው ሰው ይስተካከላሉን

وَلِلَّهِ غَيْبُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ وَمَا أَمْرُ السَّاعَةِ إِلَّا كَلَمْحِ الْبَصَرِ أَوْ هُوَ أَقْرَبُ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ

በሰማያትና በምድርም ያለው ሩቅ ምስጢር የአላህ ነው፡፡ የሰዓቲቱም ነገር (መምጣቷ) እንደዓይን ቅጽበት እንጂ አይደለም፡፡ ወይ እርሱ ይበልጥ የቀረበ ነው፡፡ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፡፡

وَاللَّهُ أَخْرَجَكُم مِّن بُطُونِ أُمَّهَاتِكُمْ لَا تَعْلَمُونَ شَيْئًا وَجَعَلَ لَكُمُ السَّمْعَ وَالْأَبْصَارَ وَالْأَفْئِدَةَ ۙ لَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ

አላህም ከእናቶቻችሁ ሆዶች ምንም የማታውቁ ሆናችሁ አወጣችሁ፡፡ ታመሰግኑም ዘንድ ለእናንተ መስሚያን ማያዎችንም ልቦችንም አደረገላችሁ፡፡

أَلَمْ يَرَوْا إِلَى الطَّيْرِ مُسَخَّرَاتٍ فِي جَوِّ السَّمَاءِ مَا يُمْسِكُهُنَّ إِلَّا اللَّهُ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّقَوْمٍ يُؤْمِنُونَ

ወደ በራሪዎች በሰማይ አየር ውስጥ (ለመብረር) የተገሩ ሲኾኑ (ከመውደቅ) አላህ እንጂ ሌላ የማይዛቸው ኾነው አይመለከቱምን በዚህ ውስጥ ለሚያምኑ ሕዝቦች በእርግጥ ተዓምራቶች አሉ፡፡
593 views ⚘يارب خفف ه‍مي ووجعي فاُنت وهحدك تحلم بحالي وم يجري بنفسي وك يو, 18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 19:43:17 Watch "የነብዩ ሙሀመድ ሙሉ የህይወት ታሪክ ክፍል 1/2 " on YouTube


544 views🄼🄰🄷ⓘ, 16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ