ልብሽን ምክንያት እየሰጠሽ አታድክሚዉ ዩምና ሙሀመድ እራስሽን ልክ እንደ ሙሳ ቀይ ባህር መሀል ላይ አኑሪው ከጀርባሽ ፊርአውንን እሚያክል ጠላት ወይ ችግር አለብሽ ከበላይሽ የተሰነጠቀ ባህር እሚያክል አንቺ ላይ ሊደርስ እሚችል ችግሮች ተከምረው ታይተውሻል ወደ ጎን አትይም መካከል ላይ ነሽ ብቻሽን አይደለሽም በአንቺ ስር ያሉ የብዙዎችን ህይወት ከአላህ በታች ይዘሻል ....ልክ ሙሳ ተከታዮቹን እንደያዘው ነፍሴን ብቻ አይልም ነፍሳችንን እንጂ ከእራሱ ሩህ በላይ እሚያስጨንቀው የተከታዮቹን ነገር ነው ምናልባትም አንቺ የብዙ ሀላፊነት ባለቤት ሆነሽ ይሆናል፡፡ ታዲያ ሙሳ ከባህሩ አልወጡምን? በየትኛው መንገድ? ከፊት ለፊታቸው በምትታያቸው አንድ መንገድ ያቺን መንገድ እስኪያገኟት ድረስ ወደ ሗላ አልዞሩም ወደ ሗላ ችግራቸው ነው ያለው ፊት ለፊታቸው ግን ነፃነት ከብዙ የነፍሶች ሀላፊነት ማረፍ ሀቀኝነትን ብቻ ቡዙ ተአምሮችን ይዟል ያቺ የታየቻቸውን መንገድ በጀሊሉ ፍቃድ ደረሱባት ዞር ብለው ወደ ችግሮቻቸው ሲያዩ ግን ቢወርድ ሊያጠፋቸው እሚችለው ባህር ሲከተላቸው የነበረውን ችግር ድምጥማጡን አጠፋላቸው አንቺም ያሉብሽን ችግር እስክታልፊያቸው ዞረሽ አትመልከቻቸው ይደርሱብኛል እምትያቸው ችግሮችሽ ምናልባት የደረሱብሽን ችግሮች ማጥፊያ ናቸው ፡፡ መውጫሽን ተመልከቺ ግን ስለሁሉም ጌታሽን አጥብቀሽ ያዢው በእሱ ያለሽ እምነት ከልብሽ አድርጊው የተፃፈልሽ ሙሲባ በሙሉ ሊስትሽ አልነበረም የሳተሽ በሙሉ ሊያገኝሽ አልነበረም ልብሽን ምክኒያት እየሰጠሽ አታድክሚው ☞ አንቺ ማለት ሳትጠይቂው ለእሱ ባሪያው እንድትሆኚ የፈጠረሽ ባሪያው ነሽ ☞አንቺ ማለት ከስንት ሚሊዮን እህት እና ወንድሞችሽ ተመርጠሽ የተፈጠርሽ ፍጡር ነሽ ☞አንቺ ማለት በዱንያው እሳት ፈትኖሽ እንደ ወርቅ ሊያስከብርሽ ሊያስወድድሽ እሚያደርግ ጌታ ነው ያለሽ >>> እናም ያኡኽታ ረህማኑን አጥብቂው የተጣበቀብሽ ይለቅሻል 723 viewsedited 12:08