አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ የታሪኩ ርዕስ #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት #ክፍል ☞ አስራ ስምንት ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ ሚፍታህን አሳማኝም በሆነ የማያሳምን የተለያዩ ለፀብ ለቁርሾ የሚሆን ስበብ ፈልጌ አንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ልርቀዉ ወሰንኩኝ ......... በተለያዩ ዘዴዎች አዉቄ ሁለታችንን ሊያጣላን የሚችል ጥፋት እያጠፋሁ ነገር እየፈለኩት በራሴ ጥፋት ሚፍታህን መጣላት ጀመርኩኝ....ግን በተጣላን ማግስት ሚፍታህ ከቤቴ ስወጣ መንገድ ላይ እየጠበቀ በራሴ ጥፋት ይቅርታ አርጊልኝ ይለኛል በተለያዩ ዘዴዎች የዉሸት ምክንያቶች እየደረደርኩ ብዙ ጊዜ አስቀየምኩት ግን ሚፍታህ ይቅርታ አርጊልኝ እያለ ሊርቀኝ ከኔ ተስፋ ሊቆርጥ በጭራሽ አልቻለም..... ከትንሽ ቀን ቡሀላ ሚፍታህ ለስራ ጉዳይ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ ፡፡ አሁን ሚፍታህን በአካል አላገኘዉም በስልክ ብቻ ነዉ የምንገናኘዉ...ለመለያየት ከኔ ተስፋ ለመቁረጥ ጥሩ ጊዜ ነዉ ብየ አሰብኩኝ ...ለእኔም ለሚፍታህም የሚጎዳ ከባድ ዉሳኔ ወሰንኩኝ.... ሚፍታህ ከልቡ ቆርጦ እንዲጠላኝ ስልኩን block አረኩት ... ምክንያቱም እሱን ባወራሁት ድምፁን በሰማሁት ቁጥር የበለጠ እየወደድኩት እያፈቀርኩት መሀባዉ እየጨመረብኝ ሄደ ፡፡ ደግሞ በዚህ ሁኔታ ሁኜ መለየት አቅቶኝ እያለቅሱኩኝ ከዚህ በላይ ደግሞ ብወደዉ አብጄ ልብሴን መቅደዴ አልቀረም. ፍቅር ግን ምንድን ነዉ የበፊት ምርጥ ትወልዶች፡ፍቅርን እንዴት ነበር የገለፁት??? መጀመሪያ የፍጡራን ፈጣሪ የሆነዉን የአለማት ጌታ ለአላህ ነበር ፍቅራቸዉ..እስኪ የዚችን ንፁህ ልብ ያላት ወጣት የፍቅር ታሪክ ልጋብዛችሁ ★★★ ኡመር(ረ.ዐ)በመዲና ጎዳናዎች ላይ በጨለማ ሲዘዋወሩ አንድ ቤት አጠገብ ሲደርሱ እናት እና ልጅ ሲከራከሩ ይሰማሉ እናት፡-ልጄ ሆይ ነገ ከምንሸጠዉ ወተት ላይ ጥቂት ዉሀ ጨምሪበት ልጅ፡-እማዬ ኸሊፋዉ ኡመር ወተት ላይ ዉሀ እንዳንጨምር ከልክለዉናል ትላታለች እናቷን እናትም፡-ኸሊፋዉ እኮ አሁን የምንሰራዉን አያየንም አለቻት ልጅም፡ አላህን በመፍራት ለእርሱ ባላት ፍቅር ልቧ የተሳበዉ ወጣት እንዲህ አለቻት ..እናቴ ሆይ!!!ይህን ድርጊታችንን ኸሊፋዉ ባይመለከተንም ከአላህ ግን ልንደብቀዉ አንችልም አለቻት፡፡ ልጅቱ ለእናቷ የሰጠቻት መልስ ኡመርን በቆሙበት ቦታ በሲቃ ናጣቸዉ፡፡ ከዛም ሲነጋ ቤቱ የማን ቤት እንደሆነ አረጋግጠዉ ያቺን ልጃገረድ ልጃቸዉ እንዲያገባ ሁኔታዉን አመቻቹለት፡፡ ምክንያቱም ልጅቱ ለአላህ የነበራት ፍራቻ ከርሷ የሚጠበቅ አልነበረምና፡፡ ከእነዚህ ጥንዶች የተወለደዉ በኢስላም አምስተኛዉ በትክክል የመራ ኸሊፋ እንደሆነ የተመሰከረለት ኡመር ኢብኑ አብደል አዚዝ የተገኘዉ፡፡ እናቱ አላህን ፈሪ ስለሆነች በዛ ተርብያ ስላሳደገችዉ ለዲነል ኢስላም መሪ የሆነ ልጅ አበርክታለች....እንደዚህ ለአላህ የነበራቸዉ ፍቅር ላይ ያለፉ ትዉልዶች ስንት ስቃይ አሳልፈዉ እኔ ግን በሚፍታህ ፍቅር እርብሽብሽ ለቅሶ በለቅሶ ሁኛለሁ ... እኔም እንዲህ ብየ አሰብኩኝ >>>> #ትዳር_ለኔ_አልተፈጠረም_ቢክራ_ስላልሆንክ_የወደድኩትን_ሰዉ_ማግባት_አልችልም