Get Mystery Box with random crypto!

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዋስትና ታገዷል ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከእስር እንዲፈታ ወይም የማ | ሁሌ አዲስ ሚዲያ (Hule Addis Media)

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዋስትና ታገዷል

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከእስር እንዲፈታ ወይም የማይፈታበትን ምክንያት ካለ ችሎት ቀርቦ እንዲያስረዳ ታዞ የነበረው አዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን ዛሬ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 1ኛ ፀረ ሽብር ችሎት ቀርቦ፣ የዋስትናው ብይን በፌደራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት የታገደ ስለሆነ ሊፈፅም ያለመቻሉን አስረድቷል።

ችሎቱም ያልተፈታበትን ይሄን የጠቅላይ ፍ/ቤት ምክንያት ተቀብሎ አሰናብቶናል።

በዚህ መሠረት ጠቅላይ ፍ/ቤት፣ ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በዋስትና ሊፈታ አይገባም ክርክር ላይ ይግባኙን ለማድመጥ ለሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ቀጠሮ ሰቷል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ላይ መንግስት በምጥ ያዋለደው ወንጀል በፍርድ ቤት ዋሰትና ቢፈቀድም እንቢተኛው ፖሊስ አልፈታም ብሎ ሠንብቷል::ዛሬም አቃቤ ህግ ይግባኝ ብሏል በማለት የፌደራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ዋስትናውን አግዷል::


የሁሌ አዲስ ሚዲያ ፈጣን መረጃዎችን በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ባሉበት ሆነው ይከታተሉ፤
Facebook : https://www.facebook.com/Huleadissmedia/
Telegram : https://t.me/Hulaadiss
YouTube Channel
https://www.youtube.com/channel/UCk934znIu60LV3czcIVZ9Bg
Twitter: https://twitter.com/Huleaadis_Media?