Get Mystery Box with random crypto!

📚منهج السلف طريقن الى الله 📚

የቴሌግራም ቻናል አርማ htt_asselfya — 📚منهج السلف طريقن الى الله 📚 م
የቴሌግራም ቻናል አርማ htt_asselfya — 📚منهج السلف طريقن الى الله 📚
የሰርጥ አድራሻ: @htt_asselfya
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.81K
የሰርጥ መግለጫ

#ወደ ኃላ እራስህን አግኝ።
#ይቀላቀሉን ለሌችም ሸር ያድርጉ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
https://t.me/htt_asselfya

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 22:30:36 ምርጥ. ሚስት ..

አንድ. ሸይኽ እንዲህ አሉ
[ ብናውቅ ኖሮ በእናታችን ሆድ ውስጥ ሆነን መልካም ሚስት ስጠን ብለን እንለምን ነበር ብለዋል። ]

ተወልደን አድገን አልፎም ያገባው ስለመልካም ሚስት ዱአ  ሊዘናጋ አይገባም።
ምድር ካስተናገደቻቸው ምርጥ ሚስቶች መሐከል፦


ዛሬ ባለትዳሮች መሐከል ይህ ድርጊት ታደርጋለች ተብሎ ባይታሰብም የነብዩ ባለቤት አይሻ
( አሏህ ስራዋን ይውደድላትና)
እንዲህ ነበረች ፦
[ የመልክተኛው ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ልብስ እርጥብ
መንይ በነካው ጊዜ አጥብላቸው ነበር መንዩ ደርቆ ከሆነ

እፈቀፍቅላቸውና ይሰግዱበት ነበር ] ብላለች።
~ አይሻ ሳትጠየፍ ሳታፍር ሰርታ ያለፈችው ዛሬ በኢልም ማዕዶች ላይ ስለዚህ ርዕስ ሲወራ
ወንዶችም

መሽሞንሞናቸው ሴቶች አይን አውጣ እባለለሁ ይሁን ብቻ አላውቅም ከሀቅ ያፍራሉ ።


~ አይሻ እድሜዋ ከ ነብዩ ሲጋቡ ዛሬ በሰፈራችን የሚጫወቱ ህጻን አይነት እድሜ ላይ ነበረች
~ አይሻ ውዱ ነቢይ ወደ አኼራ ሲሄዱ እድሜዋ 18 ዛሬ ለትዳር ለማጨት ስትጠይቅ እድሜዋ አልደረሰም ብለው
እንደሚሸኙ አይነት ነው


~ አይሻ ከ 9 እስከ 18 አመት ባለው እድሜዋ የመልክተኛው የጀርባ አጥንት ሆና አለፈች ዛሬ አላህ ያዘነላቸው ሲቀር በሆነ ባልሆነው የምትነዘንዝ በዝተዋል


~ አይሻ በዛች እድሜዋ የሰራቻቸው መልካም ስራዎች የተጎነጨችው ኢልም ዛሬ የእኛ እህቶች መሬት ወርደው

እንደ ሚዳቆ በገመድ ዝላይ እና ሰለጠኑ ከተባለ በቀለም አሸብርቆ በታኮ ጫማ ልታይ ባይነት ያሳስባቸዋል

~ አይሻ ከመልክተኛው ጋ ከአንድ ወር በላይ ቤታቸው እሳት ሳያቀጣጥሉ እንዲሁም የሚበላ አጥተው አሳልፈዋል የእኛ እህቶች ዱንያ ዘውታሪ መስሎዋቸው ይሁን ብቻ አላውቅም እቃ ቤት ውስጥ  አስቤዛ ካልተከማቸ ይሉሃል

~ አይሻ ከነቢያችን ጋር ስታሳልፍ ተደራራቢ ብፌ፣ አረቢያ መጅሊስ፣ ዘመናዊ ማንኪያ፣ ጭልፋ ፣አልጋ እንዲ አይነት፣ፍራሽ ካልገዛህ አላለችም ዱንያ አላፊ መሆንዋን ተረድታ የነበረው የዘምባባ ኬሻዋን አበጃጅታ ይተኙበት ነበረ

~ አይሻ እንደ ዛሬ ቀለም ሰራተኛ መስለው ወጥተው ከሚታዩ ሴቶች በተቃራኒ ከደሳሳ ጎጆዋቸው መውጣት

አታስበውም ነበር የዛሬዎቹማ ኒቃብም ለብሰው ኒቃባቸው ከፍተው ሲመገቡ ካፌ ላይ ይታያሉ ___ከአይሻ ያለው
እርቀት !!

~ አይሻ የእኛ እናት የረሱል ሚስት.    የትዳር ምርጥ ተምሳሌት
[ የነብዩ ሙሐመድ አለይሶላቱ ወደሰላም ምርጥ ሚስታቸው ነበረች  ]
ልጠቅልለውና


ጥሩ ሚስት እያልክ ስትቦርቅ የመልክተኛው ባህሪ ሙሉ
ስብዕና ለሚስታቸው ምን አይነት እንደነበሩ ማወቅ
መልካም ሴት ከመፈልግ ይቀድማል ብዬ አምናለሁ።


https://t.me/umufwzan
https://t.me/umufwzan
70 views19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 19:39:30 አድስ የኪታብ ደርስ
⇡⇡ #ኪታብ_ሪያዱ_ሷሊሂን ⇡⇡
ማብራሪያ
በኡስታዝ ኢሊያስ አወል (ሀፊዘሁሏህ)

ክፍል
ፔሌግራም ቻናል

https://t.me/AbuSalihAlosimine
103 views16:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:01:59 #የወሎ_ልጅ_አብሽር_!!
---------------------------------
አንዳንዴ ተናገር ግድ ፃፍ ይለኛል፡
ሙስሊሙ ሲነካ ሲጠቃ ያመኛል፡
ልቤ ከነርሱ ጋር ጭልጥ ይልብኛል፡
እምነቴ ሲደፈር ውስጤን ይነዝረኛል፡
ወተት ነህ እያሉ አልበውት ሲያበቁ፡
ዛሬም ያሴራሉ እየተደበቁ፡

በኛ ሸፍጥ ሰርተው ፊኛ ቢወጠርም፡
ወሎዬ በፍርሀት አይጠረጠርም፡
ጀግና ልጅ እያለው ክብሩ አይደፈርም፡
ዳግም ለህውሀት ወሎዬ አይገብርም፡
ነጋሪት ተመታ ማንም ተደለቀ፡
የወሎ ልጅ ቆርጧል አይሆንም አለቀ።

-------------------------------------------
ደሙ እየፈሰሰ ንብረቱን ተዘርፎ፡
በሙስሊምነቱ ሁሌም ተወርፎ፡
ማንም ሲዝትበት እሱን ብቻ አኩርፎ፡
በሁሉም አቅጣጫ ወሎ አሁን ተነስቷል፡
መሸሹ ቀረና ወደ ግንባር ዘምቷል፡
እምነቴን ለመድፈር ከቤቴ ከመጣህ፡
ታሪኩን ልትደግም ወገኔን ካቃጣህ፡
ምናለ ይህ ፀሀይ ለአንተ ሲል ባልመሸ፡
እንዳትጠራጠር እጥፍ ነው ምላሸ፡
ተቀባብሏል አብሽር ፅዱ ነው ክላሸ፡

--------------------------------------------
የወሎ ጀግና #ያ_ሽርጥ ለባሽ፡
ያዘጋጂሻል እንደሚገባሽ፡
ለግፍሽ ሁሉ ይሰጣል ምላሽ፡
ወሎን አትንካ እንዳትበላሽ፡

በፍቅር ባደጉት በሀላል ልጆቿ፡
ትኮራለች ወሎ ሁሌም በጀግኖቿ፡
#ደምሌን ተመልከት #የጊራናን ነብር፡
#ከከረሙ_ልጅ ጋር #ምሽጉን_ሲሰብር፡
የእስላም ልጅ ታማኝ ነው አይገዛም በብር፡
የትግራይ ሙስሊሞች እኛን አልተዋጉም፡
ፍፁም ሰላም ናቸው መጥፎ አላደረጉም
፡
ለወሎ ልጅ ትግሬ መቼም አያሰጋም፡
ምን ሴራ ቢቆመር መንገዱ ቢዘጋም፡
መድፍ ስናይፐር መትረየስ ቢተኮስ፡
ህዝቡ እንዳይገናኝ እሾህ ቢቸረኮስ፡
ትግራይና ወሎ አይነጣጠልም፡
ፍቅር ዘምሮ እንጂ በቂም አይቀጥልም፡

--------------------------------------------
የትግራይ የወሎ መሪር ጠላታችን፡
ህውሀት ብቻ ነው ችግር የህዝባችን፡
ሀያ ሰባት አመት በመከራ አኑሮን፡
ካላጠፋሁ ብሎ አሁን ደግሞ ወሮን፡
መድፍ ከተኮሰ ብሎ ወሎን ላጥፋው፡
ወሎ ተነስና ከመጣበት ግፋው፡
ተነስ ተጠራራ ሀገርክን አስከብር፡
አግስተህ ውጣበት ዘለህ እንደ ነብር፡

------------------------------------------
ጀበርናውን ለብሶ ክላሹን ወልውሎ፡
ፈገግ ይላል ፊቱ ከጦር ግንባር ውሎ፡
ፍቅር ጀግንነት ጋር እንደዚህ ነው ወሎ፡

ደረቱን ለጥይት እየገለበጠ፡
ጠመንጃ ይነጥቃል እርሳስ እንደዋጠ፡
➻#አብሽር_ወሎ___!!
ይሄ ነው ታሪኩ አይንበረከክም፡
ደፍሮ ለወረረው ሽማግሌ አይልክም፡
ለሀበሻ ምድር ወሎ ደም ገብሯል፡
እየተጨቆነ ፍቅር አስተምሯል፡
ተፈናቅሎም ደግሞ በየቦታው ሰፍሯል፡
ወሎ ከባንዳወች አልተፈራረመም፡
ለዚህም ነው መሰል ጭቆናው አልቆመም፡
#አብሽር_ወሎ__!!

ማንንም አልነካን ከምኑም የለንም፡
መጥቶ ከወረረን አማራጭ የለንም፡
ከደቡብ ከሰሜን ከሁሉም አቅጣጫ፡
ከምዕራብ ከምስራቅ አይኖርም ማምለጫ፡
የአክሱም ሙስሊሞች ዱዐ አድርገውብህ፡
አሏህ ፀሎት ሰምቶ ወሎን አስነሳብህ፡
የትግራይ ሙስሊሞች አብሽሩ አይዟችሁ፡
#አሏህ#ክፉ አይሰራም በርቱ በዱአችሁ
፡
➻#አብሽር_ወሎ___!!
የጦለሀ ጀዕፈር የአባ ጂፋር ወንድም፡
ወሎ በታሪኩ ባንዳ ልጅ አይወልድም፡
በእምነትና ባገር ፈፅሞ አይቀልድም፡
ፈሪና ሰላቱ በጭራሽ አይወድም፡
የአርሹ ባለቤት አሏህ ከፈቀደ፡
ጌታችን ከረዳን እሱ ከፈረደ፡
#ደብረ_ፂወንና_ጌታቸው_ረዳ፡
በወሎ ራያ ላይ ይሆናሉ ፊዳ፡
ትግራዋይ ወገኔ አይገርም ታፍኖ፡
ምኞቴ ነው እኔ ማየት ሰላም ሰፍኖ፡
➻አብሽር_ወሎ__!!

በአሏህ እገዛ በጀሊሉ ጉልበት፡
ሰላም ይሁን ሀገር ብዙ ግፍ አለበት፡
#ወሎ_በጀግኖቹ_ይከበራል_አብሽር፡
#ሀገሩ_ተደፍሮ_አይወጣም_ሽርሽር፡
#አንግቶ_ይዘምታል_ያባቱን_ሚኒሽር፡
በተግባር ተመልከት ያን ጀግና ሽርጣም፡
ምሽግ ሰባሪ ነው ሳያወልቅ ጥምጣም፡
ወሎ በፍቅር እንጂ በፀብ አያዋጣም፡

የአሏህ ስጦታ ነው ምድሩ ጀግና አያጣም፡
ወሎን አትሳደብ #ይተዋል ጫት መቃም፡
ጠላቱን ብቻ እንጂ በዘር አያጠቃም፡
ወሎ የሀገሩን ልጅ ሀሽሽ አያጠጣም፡
ስትነካኩት እንጂ ለማጥቃት አልመጣም
፡
▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴
#አብሽር_ወሎ__!!
የሚመረትበት ፍቅር ሻይ በዳቦ፡
ወደ ግንባር ሔዷል ዘምቷል ወረባቦ፡
ወሎ አሁን መሮታል ሰሜኑም ደቡቡ፡
መጥተዋል ሊገርፉህ ትጥቅ እንዳነገቡ፡
ሴራህን አክሽፈው ሰላም ለመገንባት፡

አቅፈው ሊዘይሩ የ#ትግራይን አባት፡
በጭካኔ ይዘህ አንተ ስታፍናት፡
ካንተ ሊለያዩ የ#ትግራይን እናት፡
የ#ወሎ_ኦሮሞ የጦር ጠበብቶቹ፡
ወደ ራያ ግንባር ዘምተዋል ጀግኖቹ
፡
ከነፋሪስ ሀገር ከጅሌ ጥሙጋ፡
ዘምቷል የወሎ ልጅ ወሎን ሊያረጋጋ፡
ያንን የሀገር ጠላት ሊገርፈው በአለንጋ፡
ከባቲ ከሚሴ ከአርጡማ ፋርሲ፡
ተሟል የወሎ ልጅ #ጂርቱ እያለ #አከሲ፡
የወሎ መከራ ያንቀጠቀጣቸው፡
ቀጠን ቀጠን ያሉት ጀግንነት መጧቸው፡
የወሎ አናብስቶች መጡ ጠብቃቸው፡
ጀግና ናቸውና ፍፁም አይፎክሩም፡
ለፍቅር ነው እንጅ አያቀረቅሩም፡
ታሪኩ ይናገር ጠላት አያከብሩም፡
ምሽግህን ሰብረው ሳይገርፉህ አይቀሩም፡
➻#አብሽር_ወሎ__!!
ወሎን አያውቀውም ቀረርቶ ፉከራ፡
#ቢበዛም_ጠላቱ_ቄስና_ደብተራ፡
ሁሉን አስተናግዷል ፈቅዶ በየተራ፡
ሀገሩን በመሸጥ ወሎዬ አይታማም፡
ልቡ ተራራ ነው ማንንም አይሰማም፡
የጦር ሜዳው ንጉስ በልበት ሽርሽር፡
አሏህ ይከተልህ የወሎ ልጅ አብሽር
፡
▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴
        #በኑረዲን_አል_አረቢ
▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴
http://t.me/nuredinal_arebi
http://t.me/nuredinal_arebi
111 views10:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 21:48:38 አድስ የኪታብ ደርስ
⇡⇡ #ኪታብ_ሪያዱ_ሷሊሂን ⇡⇡
ማብራሪያ
በኡስታዝ ኢሊያስ አወል (ሀፊዘሁሏህ)

ክፍል
ፔሌግራም ቻናል

https://t.me/AbuSalihAlosimine
183 views18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 19:15:48
➻እህት አለሜ ጓደኛ ካለችሽ?!

➝ጓደኝነት ለአሏህ ብሎ መዋደድ?!እናማ የኔ እህት ላስታውስሽ የምፈልገው ሁሌም ለአሏህ ብላ በእሱ መንገድ ብቻ ና ብቻ የምትወድሽ በኸይ ነገር የምታስታውስሽ መርጥዬ ጓደኛ ካለችሽ አጥብቀሽ ያዣት!!
     ◆◉                   ◆◉     
⓵ወደጃት አክቢሪያት አታሪቂያት!
❷ወሬ ስታወራሽ አዳምጫት ተረጃት ለቃሏ መልስ ስጫት...!
❸ቃልሽን አክብሪ አታታሊያት አትዋሻት
❹ሚስጥር ብላ ያወራችሽን ሚስጥሯን ጠብቂላት!
    ➻ለአሏህ ብለው መዋደድ
⓵ወሬ በምላስ ብቻ የሚተረክ አይለም።
❷በዲኒያ ጥቅምየማመሰረት አይደለም።
❸በመካከላችን በዘር:/በብሄር:/ጥርጣሬን ማስቀመጥ አይደለም።

❹ሰው ነን እና?በመካከላችን ስህተት ይፈጠራል መዘጋጋት:መራራቅ:በብሎክ መሸኛኘት አይደለም።
➝ለአሏህ ብለን ከወደድን ውደታችን ከምንም ከዱኒያ ጣጣጋ ጥቅም አይሄድም አይገናኝም።
      ➻አሏህ ይዘንልን እና!
➝በዚህ ጊዜ እከሌ ጋርኮ ጓደኛ ነበር ትቻታለሁ....የተለያየንበት ጉዳይ ግን?
نسأل الله السلامة
والعفية
➻ለአሏህ ብሎ መውደድ ምን እነደሁ እንወቅ እንተግብር እንዋደድ።
➝ለአሏህ ብለው የማወዱ ምርጥየ ጓደኞችን ያብዛልን ለእሱ ብለን የምንዋደድ ያድርገን ንግግራችን ከተግባራችን የገጠመ ያድርግልን አሚን))

https://t.me/umufwzan/5618
https://t.me/umufwzan/5618
147 views16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:12:49 ጥቂት ነጥቦች ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ
~
1.  ወገኔ ሆይ! አገርህን አትልቀቅ።

ባለፈው ተፈናቃዮች ላይ የደረሰውን አስታውስ። ደብረ ብርሃንና ባህርዳር ለተፈናቃዮች ከማጎሪያ ካምፕ የማይለዩ እንደነበሩ ሲወራ ነበር። አሁን ደግሞ ነገሮች ከቀድሞው ቢብሱ እንጂ የተሻሉ አይደሉም። ፖለቲከኛውን ተወው። ህዝብ እራሱ ኑሮ ስለከበደው ሊጨካከን፣ ሊሰላች ይችላል። ሩቅ አትሂድ። ደሴ ወልዲያን፣ ወልዲያ ቆቦን ሊሰለች ይችላል። የጎደለበት ደግሞ በትንሽ በትልቁ ይከፋዋል። ስለዚህ በተለየ እፈለጋለሁ ብሎ የሚሰጋ ካልሆነ በስተቀር ጦርነቱ ቀጥታ ከሚካሄድባቸው ቀጠናዎች ለጊዜው ዞር ከማለት ውጭ ካገር ርቆ መሄድ ስቃዩን የከፋ ያደርገዋል።

2.  ወገኔ ሆይ! ንብረትህን ጠብቅ።

ሩቅ ብቻ አትመልከት። እዚያው በዙሪያህ ለዘረፋ ተደራጅተው ከግለሰብ ንብረት እስከ ተቋም ሲዘርፉ የነበሩ እንደነበሩ ይታወቃል። ዛሬም ይኖራሉ። ፍሪጅና ቴሌቪዥን ሳይቀር በግመል እየጫኑ የወሰዱ የገጠር ሰዎች እንዳሉ ሰምቻለሁ። “መብራት የላችሁ ምን ያደርግላችኋል?” ሲባሉ “እንሸጠዋለን” ሲሉ ነበር። ስለዚህ ቅድሚያ ለህይወት ጥንቃቄ ካደረግክ በኋላ በቅርብህ ሆነህ በተቻለህ መጠን ንብረትህን ተደራጅተህ ጠብቅ።

3.  ወገኔ ሆይ! ለፈተና እራስህን አዘጋጅ!

ወደድንም ጠላንም ፈተና ላይ ነው ያለነው። መጠኑ ከህዝብ ህዝብ በእጅጉ እንደሚለያይ ግልፅ ነው። ፈተናው ምን ያህል እንደሚዘልቅም አናውቅም። የሆነች ያክል የምንዘጋጅባት ሰበብ ካለችን ባለችን መጠን ለሚመጣው ሁሉ ራሳችንን እናዘጋጅ። ምግቡ፣ ወፍጮው፣ ባንኩ፣ መብራቱ፣ ቴሌው፣ መድሃኒቱ፣ ... ብዙ ነገር ይቸግራል። እስካሁንም ብዙ የተፈተነ አለ። ልዩነቱ ብዙ ባይሆን እንኳ የተዘጋጁበትና የተዘናጉበት ፈተና አንድ አይደለም። አላህ ለሁሉም ፈረጃውን ያቅርብልን።

4.  ወገኔ ሆይ! ጊዜ አይተህ አትለወጥ!

ለሚያልፍ ቀን ትዝብት ላይ አትውደቅ። የትኛውም ቡድን አጠቃኝ በሚል ማመሃኛ ማንንም ብሄር ለይተህ እንዳታጠቃ። የአማራ ህዝብ ሆይ! ህወሓትን መነሻ አድርገህ ለፍቶ አዳሪ ትግሬን አታጥቃ። “ያው ናቸው” ከሚል ስሜት ወለድ ሂሳብ ራቅ። “ህወኃት እከሌን አካባቢ የተቆጣጠረው ተፈናቃይ ትግሬዎችን ተጠቅሞ ነው” እየተባለ የሚናፈሰው ብታምንም ባታምንም ከንቱ ውሸት ነው። እንዲህ አይነት አሉባልታ ይዘህ ደካሞችን እንዳትጎዳ።
ትግሬው ሆይ! ህወኃት ሲገባ ጠብቀህ አደባባይ ለጭፈራ አትውጣ። ጠቋሚ፣ አፋኝ፣ አሳፋኝ ለመሆን አትሞክር። ሃይማኖት ወይም ሞራል እንኳ ባይገታህ ቢያንስ ለራስህ ፍራ! ነገሮች የተቀያየሩ እለት መግቢያ ታጣለህ። በባለፈው ግጭት አማራውም፣ ትግሬውም፣ ኦሮሞውም፣ አፋሩም ዘንድ ብዙ ደስ የማይሉ ነገሮች ሲወሩ ነበርና አላህን ልንፈራ ይገባል።

5.  ወገኔ ሆይ! ለመጣ ለሄደው አታጨብጭብ።

አንድ ኃይል አንድን አካባቢ ሲቆጣጠር ሆ ብሎ መውጣት፤ ሌላው በግሩ ሲተካ አሁንም ሆ ብሎ መነሳት ይሄ ግልብነት ነው። የሃገራችን ፖለቲካ ቂመኛና ተበቃይ ነው። እንኳን የገባበትን፣ የሌለበትንም ጊዜ ተጠግቶ ያጠቃል። ደግሞም በጣም ተገለባባጭ ነው። እዚች አገር ውስጥ ስንት አይሆንም የተባለ ነገር ሆኗል! መንግስት ትግራይን ሲቆጣጠር ህወኃት ዳግም ያንሰራራል ብሎ የገመተ አልነበረም። ህወኃት ሰሜን ሸዋ ከደረሰ በኋላ በዚያ አሰቃቂ ሁኔታ ይመለሳል ብሎ የገመተም አልነበረም። ስለሆነም ጥንቁቅ መሆን ያስፈልጋል። በሁለቱም አይንህ ዛሬ ላይ ብቻ አታፍጥጥ። በአንድ አይንህ ነገን ተመልከት።

6.  ወገኔ ሆይ! ህይወት አትርፍ።

አጋጣሚዎችን ተጠቅመው የሚጠሉትን ለማጥቃት የማያመነቱ እርኩስ ፍጡሮች ይኖራሉና ቢቻልህ ያለ ጥፋታቸው የበደለኞች ሰለባ ሊሆኑ የሚችሉ ወገኖችን አትርፍ። ከጎናቸው ቁም። በባለፈው ግጭት ህወኃት ሲገባ ጠብቀው ደካሞችን ያጠቁ ሰዎች አሉ። ከነሱ አንፃር ሲታይ ህወኃት በጣም የተሻለ ነበር። መረጃ ያለው ሰው የምለው ይገባዋል። ህወኃት ከወጣ በኋላም እንዲሁ ከየትኛውም ኃይል ጋር ምንም አይነት ንክኪ የሌላቸው ምስኪኖች ተጎድተዋል። ከተቻለን ጊዜ አይተው ከሚያጠቁ ነውረኞች አንድ ነፍስ እንኳ ብናተርፍ ዋጋው የትና የት ነው!! በቅርቡ ኦሮሚያ ውስጥ በነበረውን ግጭት የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለው አማራዎችን ያተረፉ ስንት ኦሮሞዎች አሉ። ግን አላወራንላቸውም። አማራ ውስጥ የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለው ትግሬዎችን ያተረፉ ስንት አማራዎች አሉ። ግን አላወራንላቸውም። የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለው አማራዎችን ያተረፉ ስንት ትግሬዎች አሉ። ግን አላወራንላቸውም። ሰው ማለት፣ ሰው የሚሆን ነው ሰው የጠፋለት!

7.  ወገኔ ሆይ! ወቅታዊ ግጭቶችንና ተያያዥ ጉዳዮችን ከሃይማኖት ጋር እንዳታጠላልፍ።

የየትኛውም ቡድን ደጋፊ ልትሆን ትችላለህ። የኔ የምትለው ወገን ከሌሎች በተለየ እንደተገፋ ሊሰማህ ይችላል። ግን እወቅ! ሌሎችም መሰል ህመም አላቸው። ቢቻል በፖለቲካውም ሞራል ግብረ ገብነት ቢኖርህ እሰየው። ያለበለዚያ ግን የሃይማኖት ተቋማትም፣ አስተማሪዎች እና የደዕዋ መድረኮችም አንተ በምትፈልገው መልክና መጠን እንዲያወሩ፣ የፖለቲካ ፍጭቶች ማራገፊያ እንዲሆኑ አትፈልግ። ማህበራዊ ሚዲያዎችም ላይ ሆነ መሬት ላይ እየተከተልክ በአክቲቪስት ቋንቋ እንዲያወሩ አጉል አትወትውት። ልትረዳ ቢያቅትህ ቢያንስ አደብ ይኑርህ። ከፖለቲከኛ ጋር የለመድከውን እሰጥ አገባ በየደረስክበት አትድፋ።

8. የሃይማኖት አስተማሪ ሆይ! ከመንጋው ተለይ!

ብሄርህን ተከትለህ ቅስቀሳ ውስጥ አትግባ። ሌላው አካል ለጦር ቢቀሰቅስ አንድ ሁለት ነገር ተመልክቶ ነው። አንተ ተጨማሪ አርቀህ የምትመለከትበት አላህን መፍራቱ ሊኖርህ ይገባል። ያለበለዚያ በምንህ ነው ከሌሎች የምትለየው? ኢን ሻአላህ ነገ ሰላም ይመጣል። እሱን ታሳቢ አድርግ። መንጋው ሊያግባባህ፣ ሊገፋፋህ፣ አልሆን ሲለው ሊያወግዝህ ይችላል። የፈለገውን ይበል እሱ በቀደደው አትፍሰስ። የሃይማኖት አስተማሪ ሆነው በቀጥታ የግጭት ተሳታፊ፣ ወይም ቀስቃሽ፣ ወይም ደጋፊ፣ ወይም የዘር ጥላቻ ጠማቂ የሆኑ መርዘኛ ሰባኪዎች ሁሉም ብሄር ጋር አሉ። እነዚህ አካላት ነገ ችግሩ ቢያልፍ እንኳ የማያልፍ ጠባሳ እየጣሉ ነው። ጦሳቸውም ከራሳቸው አልፎ ለህዝብ ይተርፋል። ከሃይማኖትህ ተማር። እስካሁን ካለፈው ተማር። ከሌሎች ድክመት ተማር። የትኛውንም ውሳኔ ብትመርጥ ከትችት ላታመልጥ ነገር የሰው ስሜት ተከትለህ እንዳትወስን። አላህን አስብ።
በመጨረሻም አደራ የምለው እንተዛዘን፣ እንተሳሰብ፣ ዱዓእ እናድርግ፣ ወደ ጌታችን እንመለስ። አላህ ከገባንበት መከራ አውጥቶ የሰላም አየር የምንተነፍስ ያድርገን። ኣሚን።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
179 views05:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ