2022-08-09 10:14:43
Biz Gitar:
ደራሲ ቤዛዊት ፋንታዬ (የሸዋ ልጅ)biz gitar
ሳልሳዊ
ክፍል 39(ሰላሳ ዘጠኝ)
፨የህይወት ፈተና በተለይ ህይወት ፊቷን ካዛረችብን ከባድ ይሆናል። በዕዝራ ህይወት ውስጥም ፈተናዎች ተደራረበዋል። ዕዝራ ከቀናት በኋላ እራሱን ያገኘው ሆስፒታል አልጋ ላይ ነው። ቀስስ አረጎ አይኑን ገለጥ አረገው። ወዲያው ለመጨረሻ ጊዜ እስራሱን ሳይስት በፊት የት እንደነበረ አስታወሰ። እጆቹን ማንቀሳቀስም አልቻለም እግሮቹም ልክ እንደ እጃቹ ሊታዘዙት አልቻሉም። እንባ ብቻ ከአይኑ ለጉድ ይዘንባል። ለሁለተኛ ጊዜ የሚፈልጉትን አግኝቶ ማጣት ይከብዳል። ከዛም በላይ ደሞ አካላችን ታዞ ጫኸን እሮጠን አልያም ተንፈራፍረን የውስጣችንን ስሜት ማውጣት አለመቻሉ ውስጥን ጎድቶ በጣሙንም ያማል። ዕዝራ አፉንም ለማንቀሳቀስ ጥረት አደረገ ግን ሊንቀሳቀሱ አልቻሉም። ውስጡ ያለውን ሀዘን በእንባ ብቻ እንዲያወጣው የተፈቀደለት ዕዝራ የማያቋረጥ እንባውን ለጉድ እያወረደው ነው።
፨ያለበት ክፍል በር ሲከፈት ተሰማው ዞር ብሎ በመከራ ለማየት ቢሞክረም አልቻለም። ዶክተር ማህሌት ናት። "ቀስ ብላ እንባውን ጠረገችለት እና "አዝናሁ" አለችው። ዕዝራም አይኑን ጭፍን በማረግ አመሰገናት። "በህክምና ቀስ በቀስ ትድናለህ ውስጥህን ማከም ቢያቅተኝም ለጥቂት ሰአት ላሳየከኝ ሰወዊ ትህትና ስል የምችለውን ሁሉ ነገር አረግልሀለው" ዕዝራ በዝምታ የዶክተሯን አይኖች ከማየት ውጪ ቢፈልግም መናገር አልቻለም። ቃል ከአፉ ለማውጣት ሲቸገር "ቆይ ቆይ አሁን ለማውራት ያስቸግረሀል ግን አታስብ ይሻልሀል የነረቭ ችግር ነው የያዘህ አሁን ስለነቃህ እናት እና አባትህን አስገብቼያቸው ታያቸዋለህ አስሚ እና ሀኪምም አሉ። ማን እንደሆነ አላውቅም ግን ስዩም ነኝ ያለ አንድ ጓደኛህም አለ ሁሉም በተራ በተራ እየገብ ያዩሀል አታስብ እንድትድን የተቻለንን ሁሉ እናደረጋለን" ብላው። በድጋሜ እንባውን ጠረጋለት ወጣች።
፨አንድ ጊቢ ውስጥ ሀይለኛ የለቅሶ ድምፅ ይሰማል። ለእቅሶ ላይ ከተሰበሰብት መሀል "ልጄ ልጄ ሙናዬ ልጄ እኔን ልጄ እኔ አፈር ልሁንልሽ" እያሉ የሚያለቅሱ ሴት አሉ። የሙና እናት ናቸው። "ልጄ ልጄ" እያሉ እሪሪ እሪሪ ሲሉ ላያቸው ሰው ሀዘኑ ልባቸው ውስጥ ገብቶ እንደጎዳቸው በግልፅ ይታያል። "ብቸኛዋ ልጄ እኔን እኔን እኔን" እያሉ ደረታቸውን በሀያሉ ሲደቁ አቤት ሲያሳዝኑኑኑ። ፊታቸውን ሲፎጭሩ ፤ አቅም አጥሯቸው ድክም ሲሉ ሆዳቸውን እየደበደቡ ወደ ፈጣሪያቸው አንጋጠው "ምን አረኩህ ምን በድዬ ነው እንዲህ አይነት ስቃይ ያሸከምከኝ እኔን ብትወስደኝ አይሻልም?" እያሉ ድምፃቸው እስኪዘጋ ሲያለቅሱ ላያቸው ሰው ያማል። አስተዛዛኝ ጎረቤቶች ሁሉ የሚያስለቅሳቸው ከሙና ሞት ባሻገር የሙና እናት ቃላቶች እና አለቃቀሰሰ ነው።
፨እዚህ ደሞ የመጀመሪያ ፍቅሩ መካሻ የነበረችውን ሙናን አጥቶ በእሷ መሞት ውስጥ የሚሰቃይ ሊላ ፈጥረት አለ። ዕዝራ!
እናቱ ቁልቁል ወደ ተኛበት አልጋ እያዩት እንባቸውን ያወረዱታል። "ልጄ ምን ብዬ ላፅናናህ? ልጄ ምን ቃል ነው አንተን ሊያፅናናህስ የሚችለው?" እያሉ እሪሪ አሉ። ዕዝራ እናቱን ሲያያቸው እንባው በፍጥነት መውረድ ጀመረ። የእንባው ፈሳሾች ጆሮ ውስጥ ያለ ከልካይ ጥልቅ ጥልቅ ጥልቅቅ ይላሉ። "እኔን ልጄ እኔን እኔ እንዲህ ስቅይት ልበልልህ፤እኔ እንዲህ እዝን ልበልህ ልጄ" ብለው ወለሉ ላይ ተደፍተው እሪሪ አሉ። ዶክተር ማህሌት መጥታ "እባኮትን አያስጨንቁት" ብላ ይዛቸው ወጣች።
፨እሳቸው ከወጡ በኋላ አባቱ መጡ። አባቱም "ልጄ የኔ ጠንካራ ልጅ አይዞህ ሁሉም ነገር ያልፍል ልጄ ጠንካራ ነህ አውቃለሁ ይህንንም አልፈህ ጥሩ ህይወት ትኖራለህ"ብለው እንባ ሲተናነቃቸው ወጡ። እሳቸው ሲወጡ። አስሚ እና ሀኪም ገብ። አስሚ "ዕዝራ ወንድሜ የኔ ምረጥ እባክክን በአላ አታልቅስ" አለችው። እሷ እያለቀሰች ሀኪምም "ዕዝራ ሁሉም ሰው ይፈተናል እንደነገረኩህ ያንተ ግን እንደ ሰወኛ ስናስበው በጣም ከባድ ነው። እንደ ፈጣሪ ግን ለበጎ ነው ወንድሜ አይዞህ በቃ አስሚ ነይ አናድክመው ስዩም ስላለ እሱ ብዙ የሚነግረው ነገር አለ" ብሎ አስሚን አቅፎ ይዞት ሲወጣ አሰሚ ዞር ብላ "የኔ ዕዝራ ወንድሜ በጣም እንወድሃለን እሺ" ብላው ወጣች።
፨ከወጡ በኋላ አስሚ እና የዕዝራ እናት እያለቀሱ በባሎቻቸው በመባበል ላይ ናቸው። ዶክተር መሀሌትም "ስዩም መግባት ትችላለህ" ብላ ወደ በሩ ጠቆመችው። ስዩምም ገባ። ወደ ዕዝራ ጠጋ አለ የዕዝራ እንባ አሁንም እየፈሰሰ ነው ስዩም ጥቁር በጥቁር ለብሷል በጣም እንዳዘነ ከፊቱ ያሳብቅበታል። "ስላም ዕዝራ ጓደኛዬ አንዴት ነህ መቼስ ይሄ ልጅ አንዴት ከዛ ጊቢ ወጣ ብለህ ለእራስህ እየጠየከው ነው አደል? የምነግረህን በትኩረት አድምጠኝ እሺ። እኔ ሳይካትሪስት ስዩም እባላለሁ አንተን በማዳን ውስጥ የራሴ ተልኮ ነበረኝ። ምን መሰለክ ተልኮዬ አንተ እየተሻለክ በመጣህበት ወቅት እና ሲማይን እንደረሳት ከታወቀ በኋላ በህይወት ተስፋ አለህ ወይስ የለህም የሚለውን አስተሳሰብ ለመፈተን ነው ወደ አንተ የመጣሁት ሙና አንተ ፊት በህይወት ተስፋ የቆረጠውን ማለቴ ሙናን የወጋት ሰው አወከው አደል። የእሱን አስተሳሰብና በትንሹ ወስጄ አንተ ጋር ማውራት እና ስለ ህይወት ያለህን አቋም ማወቅ ነበር ተልኮዬ ስእል ስለምስል ሙና እኔን ካንተ ጋር የምታስተዋውቅበት ስበብ ሆነ። እንጂ እኔ በጣም የማፈቅራት ሚስት እና አራት ልጆች አሉኝ። ሊላው ልነግረህ የምፈልገው ነገር የሙና ገዳይ ታውቃ በእስር ላይ ናት። አንተ እራስህን ስተህ ሙና ደሞ ሞታ ነው የተገኛችሁት እሷም እዛው ጭንቅላቷ ላይ ተኩሳ ነው የሞተችው" ሲለው ዕዝራ አይኑን በደብ ጨፍኖ ደቂቃ አስቆጠረ።
፨ስዩም ንግግሩን አላቆሙም "ማለቴ ስትከታተልህ የነበረችው ሳይኮ በሙና በጣም ትቀና ነበር። በእረግጥ የሙና በጣም የልብ ጓደኛ ነበረች ሙናን ደጋግማ አስቀይማት ሙናም ደጋግማ ይቅር ብላታለች። ግን ደሞ በድጋሜ መጥፎ መሆኖን ቀጠለች ሙና እንድትወጋ ያረገችው እና ሙናን ለማስወጋት ለወጊው የተቆለፈውን በር የከፈተችለት እሷ ነበረች። የወጋበትን ካቻቢቴ ሁሉ እሷ ናት እንደሰጠችው ለእሱ በሩን ከፍታ ከወደድካት ግደላት ያንተ አስተሳሰብ ልክ ነው ጥሩ ሰዎች እዚህ ሲኣል ውስጥ መኖር የለባቸውም ብላ ለሁሉም ነገር መነሻ የሆነችው እሷ ናት ይህንን ጭንቅላቷ ላይ ሽጉጥ ደቅና ነው የተናገረችው አያይዛም ሙናን የወጋትን ሰውዬ በመረዝ እንደነገችው እና ምንም ቢሆን እና ቢመጣ እንደማትቀየር ቅናትዋ የማይጠፋ እንደሆነና መኖረም እንደሊለባት ብትኖረም ብዙ ሰዎች በእሷ ምክንያት እንደሚሞቱ እሷ ከሞተች ግን ለሁሉም ነገር መፍትሄ እንደሆነ ሙናን መግደሉዋ በመቅፅፈት እራስዋን እንዳስጠላት እና ሙናን በጣም ስለምትቀናባት እንጂ ጠልታት እንዳልሆነ ተናግራ እራስዋ ላይ ተኩሳ ሞተች" አለ ስዩም። ከዛ ግን ስዩም "ወይኔ ሙና ጓደኛዬዬ" ብሎ እሪሪ አለ። ዕዝራ በማልቀስ ብዛት አይኑ ቀልቶ በጭስ የተጎዳ እና በጭስ ምክንያት ሊጠፋ የደረሰ አይን መስሏል። አለመናገር ይጎዳልና ዕዝራ መናገር ባለመቻሉ እጅጉን ተጎድቷል። ስዩም ዕዝራን አየው ዝም ብሎ እንባው እየፈሰሰ ነው በጣም አሳዘነው ቢችልና ሙናን የተፈለገውን መሰዋትነት ከፍሎ ከመቃብር ፈንቅሎ አውጥቶ የዕዝራን ልብ ጮቤ ቢያስረግጠው ደስሰ ይለው ነበር። ግን ትልቁ ችግር እሱ ፍጥረት እንጂ ፈጣሪ አደለም ለዛም ሙናን ከሞት
122 viewsɖąཞƙŋıɧą, 07:14