የዕጣ ማውጣት ሂደቱ ላይ በተደረገው ኦዲት በተገኘው ግኝት ዕጣው እንዲሰረዝ መደረጉ ለአመታት ቆጥቦ ባለ እድል ለመሆን እየጠበቀ በነበረው ተመዝጋቢ ላይ ሊደርስ የነበረውን ጉዳትና ኢፍትሃዊነት በማስቀረቱ የከተማ አስተዳደሩ ውሳኔ ትክክለኛ ነው:: ለተፈጠረው ችግር በቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮና በራሴ ስም ይቅርታ እየጠየቅኩ የማጣራቱ ስራ ያልተጠናቀቀ ሲሆን በቀጣይ ከከተማ አስተዳደሩ በሚሰጡ አቅጣጫዎች የምንወሰዳቸውን እርምጃዎችና ቀጣይ ስራዎች ለመፈፀም የምንተጋ መሆኑን እገልፃለሁ:: ክብርት ያስሚን ወሃብረቢ በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ 5.5K views18:58